Bete Amhara

Bete Amhara

Monday, November 30, 2015

አማራ ነኝ እንጅ!!!!!
ከማረሻው ግርጌ፣ ከቀንበሩ ገመድ፣
ከበሮቼ ጋራ፣
ከጥቁር አፈር ጋር፣
አብሬ እምወጣ፣ አብሬ የምወርድ፣
አንበሳን ታግዬ፣
እንደ ፈረስ ወገብ፣ ቼ ብዬ የማለምድ፣
ሰማዩን አምኜ፣
ስለት የማስገባ፣ ለታቦቴ እምሰግድ፣
አማን አርገኝ ብዬ፣ ለጀማው እማረግድ፣
ምጣድ ያመሰውን፣
የጋመ ባቄላ፣
እንክክ እንክክ ብዬ፣ እጄ ላይ የማበርድ፣
አማራ ነኝ እንጅ፣
መንገድ ሰፋኝ ብዬ ፣
መንገድ ከገባ ጋር፣ ተነስቼ እማልነጉድ።
አማራ ነኝ እንጅ፣
መሬቱን አምኜ፣
አማን ኢማን ብዬ፣
ባንተው ይሁን ብዬ፣
ባንተው መጀን ብዬ፣አይኔን የማቀና፣
የጎረቤት ማጀት፣
ለምን ሞላ ብዬ፣ በሰው የማልቀና፣
ከወንድሞቼ ጋር፣
ከዘመዶቼ ጋር፣
በሌማት የምጎርስ፣ ንጣይዋን እንጀራ።
አማራ ነኝ እንጅ፣
አባይ ባጠገቤ፣ አቅፎ የሚስመኝ፣
ጣና በትንፋሹ፣ ባይኑ የሚጠቅሰኝ፣
ጎተራ እንደሁ እንጅ፣
ለወንድሞቼ ራብ፣ ማዴ የማያንሰኝ።
ልጄን በወገቤ በአንቀልባዬ አዝዬ፣
በአገልግል በሰንሰል፣
የሻገተ እንጀራ፣ ጣቢታ አንጠልጥዬ፣
ጎጆዬን ያቀናሁ፣
ቀን ከቀበሮ ጋር፣
ማታ ከጅብ መንጋ፣ ከድብ ጋር ታግዬ።
መታመን የሚሉት፣
መዋደድ የሚሉት፣
የጥቁር አፈር ቃል፣ ልቤ ላይ ተሰርቶ፣
በወንድሞቼ ላይ፣
የተጣደው በደል፣
የሚያብረከርከኝ፣
የሚያብሰከስከኝ፣ ጉልበቴ ስር ገብቶ።
አንበሳ ከጅብ ጋር፣
እኔ እበላ እበላ፣ በሆድ ሲታገሉ፣
አሞራና ውሻ፣
እኔ እግጥ እኔ እግጥ፣
እየበጣጠሱ፣ እየዘለዘሉ፣
በአጥንት ተናጭተው፣ በስጋ ሲጣሉ፣
አንተም ስጥ፣
አንተም ስጥ ፣
ብየ የማስታርቅ ፍቅር የሚርበኝ፣
እኔ ነኝ አማራ፣
እንኳንስ ወንድሜ፣
አራዊት ጫካውን፣
ድካውን ሲነጥቁት፣ የሚያንገበግበኝ።
አኔማ አማራ ነኝ፣
ሰማይ ከዳ ብዬ፣
ምድር ጦፈች ብዬ፣
የከሳው በሬዬን፣ አርጀ እማልበላ፣
ነገ አለልኝ ብዬ፣
የዘር ጃምዮየን፣
ላንዲት ርሃብ ብዬ፣ በእሳት የማልቆላ፣
በቂጣ የማልሽር፣
የአባቶቼን ግዝት፣የአባቶቼን ማላ።
አዎን አማራ ነኝ፣
ስሜ የጠገበ፣
ማርና ነጭ ጤፍ፣ ጮማና ብርንዶ፣
ባልበላም በልተሃል፣
ባልተኩስ ገድልሃል፣
ተብዬ እምጠራ፣
ተብዬ እምፈለግ፣ ፍርደኛ አጋሚዶ፣
አቤት ባይ ባተሌ፣
በሸንጎ በቀዬው፣ ስሜ ፍርድ ለምዶ።
አማራ ነኝ እኔ፣
ደብረ ግሸን ከርቤ፣
ረጅም መቋሚያ፣
እጀን ተደግፌ ታቅፌ እምወጣ፣
እንኳን የገዛ እጄን፣
አሳልመኝ ያለኝን፣
አይዞህ እያልኩኝ፣ ደግፌ እማመጣ።
አማራ ነኝ ጓዴ፣
ከጥማድ እርሻዬ፣
አምላክ የሰጠኝን፣
ጥንቅሽና ውልቢኝ፣
አሻግሬ እያየሁ፣ ማማ ተቀምጬ
አላፊ አግዳሚውን፣
ቅመሱልኝ የምል፣ ከእርሻዬ ቆርጬ።
አማራ ነኝ አዎ፣
በደረቅ ባቄላ፣በእንኩሮ መቀጣ፣
ጣዬ ሲበዛብኝ፣
ገብስ ቆሎዬ ላይ፣
ጉሮሮየን ላረጥብ፣ጠላ የምጠጣ፣
ባልበላሁት ዝልዝል፣
ባልጠጣሁት ማር ጠጅ፣ ሰክሬ እምወጣ።
በኩርማን እንጀራ፣
በድሪቶ ጋቢ፣
በእራፊ መቀነት፣ አንጀቴ ተሳስራ፣
በልቶብናል አሉኝ፣
የወንዙን እንጎቻ፣ ያገሩን እንጀራ።
ምነው ሆዴን ባዩት፣
ምነው ጎተራዬን፣ባዩት ወንድሞቼ፣
ይገባቸው ነበር፣
እነሱን ያቀናሁ፣
እነሱን ያጠገብኩ፣እኔ ተራቁቼ።
ከቶ ምን በድዬ፣ምን አድርጌያቸው ነው፣
ኧረ መጥተው ይዩኝ፣
እህል የጓሸበት፣
ወንድም የተራበ፣ ሆዴ እኮ ባዶ ነው።
ውሃ ጠማኝ ብዬ፣
ሃሩር በላኝ ብዬ፣ ከመንገዴ አልወጣ፣
እኔ አይደለሁም ወይ፣
እፍኝ ውሃ ጠምቶኝ፣
ለእኒያ ወንድሞቼ፣ ባህር የማጠጣ።
በጭብጨባ ብዛት፣
በምርቃት ግሳት፣
ሞቅ ሞቅ አይለኝ፣ወደላይ አልወጣ፣
በእርግማን ውርጅብኝ፣
በስድብ ነበልባል፣
ተሰደብኩኝ ብዬ፣ ወደ ታች አልመጣ።
ከላይ ነኝ አላልኩህ፣
ከታች ነኝ አላልኩሽ፣ አለሁ በእኩሌታ፣
ማነው የሚሰፍረኝ፣
ማነው የሚያጉድለኝ፣
ከባንዲራው ቀለም፣ ከባቶቼ ቦታ።
አዎን አማራ ነኝ፣
ጦቢያ የምትባል፣
የነፃነት ሰንደቅ፣
ያኔ ስትበጃጅ፣ ያኔ ስትሰራ፣
አንድ ላይ ሲማገር፣ የቤቷ ወጋግራ፣
እኔ አይደለሁም ወይ፣
ውሃ ልኳን ያቆምኩ፣ ወንድሞቼ ጋራ፣
እንዴት እጎድላለሁ፣
ካስቀመጡኝ መንበር፣ ካስቀመጡኝ ስፍራ።
አዎን አማራ ነኝ፣
የፈረሰ ማገር፣
የፈዘዘ ወራጅ፣
የዛለ ምሰሶ፣
እንደገና እንስራ፣
እንትከል እያልኩኝ፣
የደለቅኩት ድቤ፣
ከተሰማ ባገር፣
ከሞቀ በዃላ፣
በጅጌ በደቦ፣ በቀየው ታውጆ፣
አዳ ምን ዋጋ አለው፣
ሁሉም ሳር ይመዛል፣
ያድርበት ይመስል፣
በገፈፈ ክዳን፣ በዘመመ ጎጆ።
እረ እኔ አማራ ነኝ፣
የቦዘኔ ቃሪያ፣
የጤፍ ዱቄት ቂጣ፣
የሳማ ነጭ ወጥ፣"
የማሽላ ቆሎ፣
እንጀራ ነው ብዬ፣
እየገረገረኝ ቆርሸ፣ እምበላ፣
ጮማ ነው እያሉኝ፣
ቅቤ ነው እያሉኝ፣
ማጀቴን ያላዩ፣ ሰምቶ አዳሪ ሁላ።
አዎን አማራ ነኝ፣
አሳድረኝ ብሎ፣
ቁራሽ ስጠኝ ብሎ፣ከመጣ ከኔ ቤት
አልጋዬን የምለቅ፣
ቁልፍልፍ ብዬ፣
መደብ እምተኛ፣ በታበሰ ማጀት፣
ጦሜን የምተኛ፣
በባዶ ማድጋ፣ በተቋጠረ አንጀት።
ታዲያ እኔ ነኝ ባዳ??
እኔ ነኝ ባይተዋር???
በወንድሞቼ ደጅ፣
ሚዛን ያጎደለኝ፣ ለአይናቸው ቀልዬ፣
በአባቶቼ ማጀት፣
ሰርክ የምገፈተር፣
ና ውረድ ና ግባ፣ ና ውጣ ተብዬ።
የአባቶቹን ሃገር፣
የአርበኞቸን ርስት፣
ያንተ ቤት አይደለም፣
እያሉ ዘበቱ፣
በሽሙጥ አይናቸው፣ አባረሩኝ በቃ፣
ባዶ እጄን ሰደዱኝ፣
ያለ ስንጥር አፈር፣ ያላንዲት ጦሪቃ፣
ገፈተሩኝ ጓዴ፣
ሰው አላየም ብለው፣
በጠቆረው ሰማይ፣ ሌት በጠፍ ጨረቃ።
ይስሙ ንገሯቸው፣
ከነ ሻሾ በረት፣
ከነ ላሎ ማጀት፣
ሺ ጊዜ ቢታለብ፣ ማለቢያው ቢሞላ፣
ለስሙ ነው እንጅ፣
ፈርዶብኝ ነው እንጅ፣
በአዋዜ አይደለም ወይ፣
በእሬት አይደለም ወይ፣
ከወንድሞቼ ጋር፣ ፈትፍቼ እምበላ፣
አዎን፣
ከባዶ ሌማት ላይ፣
ከዱባ መረቅ ላይ፣
ዘመን የሚሻገር፣
እንቅብ የሚሞላ፣
ጣቢታ እየጋገርኩ፣ ተአምር የምሰራ፣
እኔ ነኝ ባንዲራው፣
እኔ ነኝ ሰንደቁ ፣
እኔ ነኝ፣ እኔ ነኝ፣ እኔ ነኝ አማራ።
ገጣሚ:- መንግስቱ ዘገዬ (ጃኖ መንግስቱ)
ከ ደሴ

https://www.facebook.com/permalink.php?story_fbid=923622881018470&id=808909555823137

ቤተ አማራ ሁለት ሶስተኛ አይኖችን ስለመክፈቱ:- ተከዜ ማዶ ባፍንጫችን ይውጣ

ቤተ አማራ ሁለት ሶስተኛ አይኖችን ስለመክፈቱ:- ተከዜ ማዶ ባፍንጫችን ይውጣ
******************************************************************
የተከዜ ማዶና ማዶ ሰዎች ለሽህ ዘመናት በወደረኝነት ገመድ ታስረው እርስ በእርስ ሲጓተቱ ኖሩ፡፡ ከመጀመሪያው መቆራኘታቸው አስፈላጊ አልነበረም፡፡ ለምን መቆራኘት እንዳስፈለገ ራሱ ግራ ነው፡፡ ቁርኝቱ አስፈላጊ ካለመሆኑ የተነሳ ለመቀራረብ ሳይሆን የተቆራኙበትን ገመድ ለመበጠስ ነበር ሳብ ጉተት ሲሉ የኖሩት፡፡ በእርግጥ ጉዳዩ የክርስትናና የንግስና ጉዳይ ነው፡፡ ከእስራኤል መጣ የተባለው ቅዱስ እቃ ለሀይማኖታዊ ጉዳይና ለንግስና ህጋዊ ተረገጥነት ማግኛ ሆኖ አገልግሏል፡፡ የዚህም ቦታ ተከዜ ወዲያ ማዶ ሆነ፡፡ ወዲህ ማዶ ያሉትም ያችን ሀይማታኖዊና ንግስናዊ ቦታ ላለማጣት፤ ከዛ ማዶ ያሉትም ያለ እነሱ ህይወት የምታቆም እየመሰላቸው ሲመጻደቁ ይሄው ለዘለአለም በወደረኝነት ገመድ ሲጓተቱ ኖሩ፡፡ የሚጓተቱት ገመዱን ለመበጠስ አልነበረም፡፡ ከገመዱ ጫፍ ያለውን ሰው ለመጣል እንጅ፡፡ በተለይ የተከዜ ሰሜን ማዶው ወገን ሁልጊዜ የደቡቡን ለመጣል ነበር ገመዱን ሲጎትት የኖረው፡፡ ገመዱ በጊዜ ተበጥሶ ቢሆን ኖሮ ያ ሁሉ ወደረኝነት እስከዛሬ ድረስ ባልቀጠለ ነበር፡፡ በብዛት በዚያ ወደረኛ ገመድ እየታነቀ ሲወድቅ የኖረው የታችኛው ማዶ ሰው ነው፡፡ ሁሉ በጁ ሁሉ በደጁ ሆኖለት ሳለ የንግስናና የዘውድ ህጋዊነትን ለመቀዳጀት ተከዜን ተሻግሮ ይሄዳል፡፡ በዛም ጦስ ተተብትቦ ታንቆ ሲወድቅ ታሪክ እልፍ ጊዜ መሰከረ፡፡ ያ እንግዲህ በአሁኑ ዘመን ስሌት ሞኝነት መሆኑ ነው፡፡ ያው ሞኙ የተከዜ ደቡብ ማዶ ሰው ነው፡፡ እምነት አስቸጋሪ ነውና ልብ በእምነትህ ማእከል ይኖራል፡፡ የተከዜ ደቡብ ሰዎችም በገሀዱ አለም የትም መሄድ ሳያስፈልጋቸው እዛው በበአታቸው መኖር ይችሉ ነበር፡፡ ግን እምነት ወደማዶ ይወስዳቸዋል፡፡ በእምነት ወንዝ ይሻገራሉ፤ በሸፍጥ ይታነቃሉ፡፡ እምነት መሞኘትን ወለደችላቸው፡፡ ሞኝነትም መታነቀን አተረፈችላቸው፡፡ የእጃቸውን እውነት ዘንግተው የሩቅ ነገርን በማመናቸው በየዘመኑ በራሳቸው የዋህነት እየተጠለፉ ሲወድቁ ኖሩ፡፡ በዚህም ተደጋጋሚ የመጠለፍ ድርጊት ያሰቡት ሳይደርሱ ህልማቸው ሳይሳካ መና ሆነው ቀሩ፡፡
አንድ ጊዜ አንዱ አንዱን ትግሬ “ትግራይን አስገድዶ መገንጠል ነበር” ይለዋል፡፡ ትግሬውም ራሱን ሲያዋድድ “ትግሬ ከተገነጠለ እኮ ኢትዮጰያ የምትባል ታሪክ የላትም፤ ምንም ናት” ይለዋል፡፡ ያኛውም “ታሪክ የምትሉትን ይዛችሁ ሂዱ፤ ከጥቅማችሁ ጉዳታችሁ ነው የባሰብን” ይለዋል፡፡ ትግሬውም “የተቋጠረ ስልቻ ሙሉ ጤፍ ከወደጫፉ ስልቻውን ብትቆርጠው ጤፉ ይፈሳል፤ ለትግራይ ከተገነጠለችም እንደዛ ነው” ይላል፡፡ ያኛውም “አይ ችግር የለውም፤ የተወሰነውን ጤፍ አፍስሰን ዝቅ አድርገን እንቋጥረዋለን” አለው፡፡ አሁን እንግዲህ የተወሰነውን ጤፍ አፍስሶ ስልቻውን ዝቅ አድርጎ ማሰር የተባለው ዘዴ ላይ ደርሰናል፡፡
ዋናው ነገር የተከዜ ደቡብ ሰው ዝንተ አለሙን ትግራይ ለምትባል አገር መስዋእት ሲሆን ነው የኖረው፡፡ በያንዳንዱዋ የትግራይ ቋጥኝና፤ ጎጥ፤ ተራራና ሸጥ ስር የአማራ አጥንት ይገኛል፡፡ ታሪክ ምስክር ነው፡፡ አማራ ለትግራይ ያልሆነው እና በትግራይ ያልደረሰበት ችግር የለም፡፡ በታሪክ ካመጡልን ያመጡብን ይበልጣል፡፡ አብዛኞቹ ያሳላፍናቸው የመከራ ጊዜያት እና አሁን የምንኖርበት የጨለማ ዘመን በትግራይ የተበረከቱልን ስጦታዎች ናቸው፡፡ ከወደ ትግራይ በኩል ለአማራ የመጣለት ጦርነት፤ ሽፍጥና ክህደት፤ በተለይ አሁን ደግሞ የዘር መጥፋትና ሁሉም አይነት የሰው ልጅ ሊሸከመው የማይችለው ስቃይ ብሎም አማራ ራሱ በፈጠራት አገር ዜግነትን ተቀምቶ እስከመዋለል ነው፡፡ ከወደ ትግራይ ጨው አልመጣለት፤ ጤፍና ባቄላ አልተጫነለት፤ ሙዝና ብርቱካን አልተላከለት፤ ማርና ወተት አልፈሰሰለት፡፡ ምንም፡፡
በዚህም ሁኔታ ውስጥ ታዲያ አማራ ጨቆነን ይላሉ፡፡ በእርግጥ ይህን ሲሉ አማራም እግዜሩም ይታዘባቸዋል፡፡ አማራ ጨቆነን የሚለው የአማርኛ ክስ ወድትግርኛ ሲመለስ “አማራ ከእግዚአብሔር ጋር በመመሳጠር ትግራይ ላይ ዝናብ እንዳይዘንብ አድርጓል” የሚል ይዘት ያለው ነው፡፡ በአለም ላይ ዝናብ እንዳይዘንብ አድርገሀል ተብሎ የተከሰሰ ብቸኛው ህዝብ አማራ ሳይሆን አይቀርም፡፡ ለእግዜሩ ሊሰጥ የሚገባን ክስ አላግባብ የተቀበለ አሳዛኝ ህዝብ፡፡ እንጅማ ለምኑ ብለው አማሮች ትግራይን ጨቆኑት ይባላል፡፡ ከጥንት እስከ ዛሬ በመላ አገሪቱ በጣም አነስተኛው የአማራ ቁጥር የሚገኘው ትግራይ ውስጥ ነው፡፡ አሁን በግድ የያዙትን የወሎና የጎንደር አማራ ሳይጨምር፡፡ ይሁንና አባቶቻችን ያንን ምንም የሌለው ምድር የራሳቸው መንግስት አካል አድርገው አቆይተውታል፡፡ ለአማራ ከከፈሉት መስዋእትነትም ለትግራይ የከፈሉት ይበልጣል፡፡ በተለይ ትግሬና ትግራይን ከጣልያን መንጋጋ ለማስጣል የከፈሉት መስዋእት በመላ ኢትዮጵያ እንኳ ተደርጎ የማይታወቅ ነው፡፡ ለምንድነው ይህን ሁሉ መስዋእት ያደረጉት ስንል መልሱ ሁለት ሆኖ እናገኘዋለን፡፡ አንዱ አንደተጠቀሰው የታሪክና የእምነት አካላችን ነው፤ የንግስና ማእከላችን ነው ብለው ስለሚያምኑ ነው፡፡ ሌላው ያለ ጥርጥር ከዚሁ ጋር ተያይዞ የሚገለጽ ለህዝቡ ፍቅር ስላላቸው ነው፡፡ አስቤ አስቤ እንዲሁም አንብቤ አባቶቻችን በትግራይ ላይ የጨከኑበትን ጊዜ ላገኝ አልቻልኩም፡፡ በተጻራሪው ከዛ አገር የሚመጣልን ግን የተጠቀሰው ህጸጽ እና ያልተጠቀሰው ብዙ ሳንካ ነው፡፡ ምን ምን እንደደረሰብን ወደታሪኩ አልገባም፡፡ ምናልባት ሌላ ጊዜ እመለሰብት ይሆናል፡፡
ከዚህ ተነስተን ቁርኝቱ መጀመሪያውንም ፍትሀዊ አልነበረም እንላለን፡፡ ከዛ ምድር የሚመጣብንን ሳንካ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ለመፍታት የሁለቱንም ሶስተኛ አይኖች መግለጥ የግድ የሆነበት ጊዜ ላይ ደረስን፡፡ የአማራ ሶስተኛ አይን ለዘላለም ተሸብቦ የኖረ እና ብቻውን ለመኖር የተሻለ እድል፤ ብቃት፤ ምክንያትና ሀብት ያለው መሆኑን አለመገንዘቡ ነው፡፡ አሁን አማራው የመጣባቸውን ታሪካዊ ሂደቶች ገልብጦ ማየት ጀምሯል፡፡ ያለፈባቸውን መንገዶች ጥቅምና ጉዳት፡ የአሁኑን ሁኔታና መጭውን ተስፋና እንቅፋት አንድ ላይ ገምግሞ የመንገድ ለውጥ ማድረግ እንዳለበት አምኗል፡፡ ያልታሰበውና ያልተሞከረው መንገድ አሁን ታስቧል፤ ሊሞከርም ነው፡፡ ከጊዜ ወደጊዜ ብዙው አማራ እየተቀበለው ነው፡፡
“ሰፊ አገር ሀያል አገር ይፈጥራል” የሚለው የአማራ የቆየ አመለካከት ብቻውን እውነት እንዳልሆነም ዘመኑ ራሱ ምስክር ሆኗል፡፡ በርግጥ በድሮው ዘመን ሰፊ ምድር፡ ሰፊ ከብትና ሌላም ሀብት የአንድ አገር ትልቅነት መሰረቶች ስለነበሩ አስተሳሰቡ ስህተት አልነበረም፡፡ አሁን ግን የቆዳ ስፋት ብቻውን ሀያል አገር እንደማያደርግ ታውቋል፡፡ ከዛ ይልቅ አንድን አገር ትልቅ የሚደርገው የሀዝብ ስነልቡናዊ እና ሁለንተናዊ አንድነት፤ ሳይንስና ትምህርት ናቸው፡፡ ለዘመናት ስናልመው የነበረውን ሀያልነት በዚህ መልኩ ከመቀዳጀት የሚከለክለን ነገር የለም፡፡ ስለዚህ ይህ ሶስተኛ አይን ማንም “እገነጠላለሁ” እያለ እኛን እያስፈራራ የሚኖርበትን ጊዜ በጠሰው፡፡ “እንዳይገነጠሉብን፤ አገር ይፈርሳል” እያልን በመፍራት ምንድነው የፈጠርነው? የመብት፤ የደህንነት፤ የልማት፤ የዜግነት መብቶቻችን በዚህ ፍርሀት ውስጥ ሟምተው ቀሩ፡፡ እነኝህን ሁሉ አስፈላጊ ነገሮች ለፍርሀታችን አሳልፈን ሰጠናቸው፡፡ ይባስ ብሎ አሁን እንደህዝብ ባለመኖርና በመኖር መሀል ሆነን እያጨበጨብን እንገኛለን፡፡ ይህ ሁሉ የመጣብን ሲወርድ ሲዋረድ ከመጣው የአባቶቻችን የታላቅ አገርነት ህልም አደራ ነው፡፡ በእርግጥ ብንታደልና ቢሳካ ኖሮ ሀሳቡ ባልከፋም ነበር፡፡ ግን አልሆነም፤ አይሆንምም፡፡ ሁኔታውን ለገመገመው ከደረሰብን የሚደርስብን ይበልጣል በጊዜ መፍትሔ ካላበጀን፡፡ እና ለዚህ መፍትሄ የሚሆነው ሶስተኛው አይን ከፋም ለማም ተገልጧል፡፡ ክብር ለአምላክ ይሁን፡፡ ሶስተኛው አይን ኢትዮጵያ የአማራ ሸክምና አደራ ብቻ ሳትሆን የሁሉም እንደሆነችና አማራ ብቻውን ፍዳ የሚከፍልበት ምክንያት አለመኖሩን ያሳየ መሆኑ ነው፡፡ እናፍርሳት ለሚለው ውትወታማ ተባባሪ ሆኖ ቢያፈርሳት በመፍረስዋ የተሻለ ተጠቃሚ እንጅ የባሰ ተጎጅ አይሆንም፡፡ ከዚህም በመነሳት የቤተ አማራ ልደት የግድ መሆኑን ያሰምራል፡፡
ሌላው ሁለተኛ አይን የትግሬ አይን ነው፡፡ ትግሬ በተለይ ወያኔ ሁሌ እያቆላመጥነው በአፉ “አገነጥላለሁ፤ እገነጠላለሁ፤ አስገነጥላለሁ” እያለ እያስፈራራ በልቡ ግን እየዘረፈ መኖር ነበር አላማው፡፡ እኛን በራሳችን የአንድ አገርነት ቆፈን ውስጥ አስቀምጦ መፏለልና መዝረፍ ነው አላማው፡፡ እያደረገው ያለውም ያንኑ ነው፡፡ አሁን ግን ሳያስቡት ሶስተኛው አይን ተከፍቷል፡፡ ይህም ሶስተኛ አይን ይህን አየ፡፡ አማራ እነሱን የሚያቆላምጥበት እና እሽሩሩ የሚልበት ጊዜ ማብቃቱን፡፡ አማራም ለጋራ አገር ብሎ እንጅ የዚህ የዚህ ራሱ ለብቻው መኖር እደሚችልና የተሻለ እድል እንዳለው አውቆ የራሱ ሶስተኛው አይን መገለጡን፤ ጥንትም፡ አሁንም፡ ወደፊትም የትግራይ እጣ ፋንታ አማራ ትከሻ ላይ የተወሰነ መሆኑን እና ብቻቸውን ለመቆም የማይችሉ መሆናቸውን እና ወዘተርፈ አወቀ፡፡ አሁን የተገለጠው ሶስተኛው አይናቸው የአማራ “ከትከሻየ ላይ ውረዱ፤ ሸክም ከበደኝ” ማለት ለእነሱ ወድቆ መፈጥፈጥ መሆኑን አሳይቷቸዋል፡፡ ዝንተ አለም በ “እገነጠላለሁ” እና “አገነጥላለሁ” ሰበብ እያስፈራሩ ተፈርቶ መኖር አይገኝ መቸም፡፡
የእነዚህ ሁለት ሶስተኛ አይኖች መገለጥ ታዲያ ቀድሞም ቁርኝቱ ሳብ ጉተት እንጅ “አንሳኝ ላንሳህ” ብቻ እንዳልነበረ አሳየ፡፡ በተለይ በምንም መልክ ላብራራው የማልችለው የሆነ ከጥንት ጀምሮ ገመዱን ጎትቶ አማራን የመጣል ጥረት እንደነበረ ነው፡፡ እስካሁን እንዴት በተደጋጋሚ እንደሆነ ሊገባኝ አለቻለም፡፡ ንባቤ እስከዛሬ 400 አመት ድረስ ወደኋላ ተጉዠ ይህ ጥረት እንደነበረ አሳይቶኛል፡፡ በእውነት ለምን ተደጋጋሚ የመጎተትና የመጣል ጥረት እንደተደረገ አልተገለጠልኝም፡፡ ይሁንና ቁርኝቱ የሆነ ችግር እንዳለበት እና እሱም አሁን መፈታት እንዳለበት ሶስተኛው አይናችን ገልጦ አሳይቶናል፡፡ ተፈጥሮም ራስዋ በትልቅ ወንዝ እና በረሃማ መሬት የከፈለችን ነን እኮ፡፡ የተፈጥሮውን መስመር ሰው ጥሶ ቁርኝት የፈጠረ ሁሉ ይመስለኛል፡፡ ተከዜ ወዲህ እና ወዲያ ማዶ እኮ የማይገናኝ ነገር ነበር ከድሮውም፡፡ ግድ የላችሁም የተፈጥሮ ህግ ጥሰናል፡፡ ተፈጥሮን መካስ አለብን፡፡ ራስዋ ያሰመረችውን መስመር እኛም እናክብረውና ድንበራችን ይሁን፡፡
የተፈጥሮን ድንበር በማክበራችንም ከተከዜ ሰሜን የሚጠቅመንና የሚቀርብን አንዳች ነገር የለም፡፡ በብዙዎቻችን ልብ ውስጥ ያለው የህዝቡ ፍቅር ነው የሚቀርብን፡፡ ያም ቢሆን የአንድ ወገን ፍቅር ነው፡፡ እኛ እንወዳቸዋለን እንጅ እነሱ አይወዱንም፤ እንዲያውም ይጠሉናል፡፡ የመጥላታቸው ምልክትም አማራ ላይ የሚያካሂዱት የዘር ማጥፋት እና ሌላ ከባባድ ወንጀል እነሱ መሆናቸው ነው፡፡ እስካሁን ድረስ አማራ ላይ የሚደረገውን የዘር ማጥፋት ሲቃዎሙ ያየኋቸው የተከዜ ማዶ ሰዎች 4 ብቻ ናቸው፡፡ ከዛ ውጭ ያለው ገና እናጠፋችኋለን እያለ የሚዝት እና እንደገና ስጦታ እንኳን ደስ አላችሁ የሚባባል ነው፡፡ በእውነት የትግራይ ህዝብ አማራ ባይጠላ ኖሮ አንድ ጊዜ አይደለም አምሳ ጊዜ አማራ ወንድማችን ነው አታጥፉት ብሎ የተቃውሞ ሰልፍ ያደርግ ነበር፡፡ እኔም አማራን እንደህዝብ ይጠሉታል ስል የራሳቸውን ልበ ደንዳናነት እንደምስክር በመቁጠር ነው፡፡ መቸም ከራሳቸው በላይ ሌላ ምስክር ልጠራላቸው አልችልም፡፡ እኛ ግን እንወዳቸዋለን፡፡ ወይም አልጠላናቸውም፡፡ እንግዲህ መለያየቱ ብቸኛ መፍትሄ እየሆነ መጥቷልና ለእነሱ ያለንን ፍቅር እንደምንም ችሎ መለያየት ነው፡፡ ጠንከር ብሎ መቻል ነው እንግዲህ፡፡ እና በሰላም እንፋታ፡፡ አለን የሚሉትን ታሪካቸውን ይዘው ይሂዱ፡፡ ቋንቋቸውን ያበልጽጉ፡፡ ሁሉንም ነገር እኛ ከቶ የምንነካባቸው ነገር አይኖርም፡፡ አለን ከሚሉት ታሪክ አንድም መስመር አንወስድም፤ የእኛን የራሳችንን ታሪክ እንመርቅላቸዋለን፡፡ የዘረፉትን ሀብትም ይዘው ይሂዱ፡፡ አንጠይቃቸውም፡፡ ያለንን ሁሉ ተጨማሪ ሰጥተናቸው ብንለያይ ለእኛ በጣም ጥሩ ነው፡፡ እኛን ከማጥፋት እናድን እና እንሸኛቸው እንጅ ሀብትን እንደገና ሰርተን እናፈራዋለን፡፡
“ጨቋኝ ብሄር” ከሚሉት አማራ ተነጥለው ለራሳቸው “በፍቅርና በተድላ ይኑሩ”፡፡ እኛም ለራሳችን እንኑር፡፡ ይሄን ለዘመናት እየጎተተ ሲጥለን የኖረ አጉል ገመድ እንበጥሰው፡፡ በርግጥ መበጠሱን መደበኛ እናድርገውና እውቅና እንስጠው ይባል እንደሁ እንጅ በዚህ 24 አመት ውስጥ ሲመነምን ከርሞ አሁን ፈጽሞ ተበጥሷል፡፡ ከአንግዲህ የሚኖረን ግንኙነት ከወንዝ ማዶ እና ማዶ እንጅ “እንዲህ አደረግከኝ”፤ “እንዲህ በደልከኝ”፤ “ፈለጥከኝ” “ቆረጥከኝ” መባባሉ ያቆማል፡፡ ፍቅር ጥሩ ነገር ቢሆንም እስኪያጠፋህ መሆን ግን የለበትም፡፡ ለፍቅር ብሎ አንድ ወይም ብዙ ሰው ሊጠፋ ይችላል፡፡ ያንን በማለትም በየዘመናቱ ስንሞትላቸው ኖረናል፡፡ ስለፍቅር ብሎ ግን መላው የራስ ዘር እንዲጠፋ መተባበር ወንጀል ነው፡፡ በተለይ የሚወዱትና ስንት የሆኑለት ሰው አንቆ ሲገድል እና ዘር ሲያጠፋ እያዩ መፍትሄ አለመፈለግ የባሰ ሀጢአት ነው፡፡ ፍቅርም የሚያምረው ሁለቱም ሲደጋገፉ ነው፡፡ አንዱ ለመጣል፤ ሌላው ለማንሳት በሆነበት ግንኙነት ውስጥ መኖር ግን ፍቅር ሳይሆን ነዝናዛ ትዳርን ይመስላል፡፡ የነዝናዛ ትዳር ደግሞ መፍትሄው ፍች ብቻ ነው፡፡ አለበለዛ በነዝናዛ ትዳር ውስጥ ከሁለት አንዱ የአንዱን አንገት በቢላ ሊቆርጠው ይችላል፡፡ ይህንንም እያየን መሰለኝ፡፡
የአማራ የመከራ ቀንበር የከበደው በውኑ ከሰማይ በወረደ እርግማን ነውን? አይደለም፡፡ የአማራ የመከራው ሁሉ ምንጭ የተከዜ ማዶ አገር ነው፡፡ የተከዜ ማዶን ሰው አብረን እንኑር ባልን፤ አንድ አገር እንሁን ባልን አይደለም ወይ ይህ ሁሉ የመጣብን? እነሱ ሄዱልን ማለት እኮ ዛሬ የምናየው ስቃይ አይኖርም ማለት ነው፡፡ ከተከዜ ማዶ አገር ህዝብ ጋር መፋታት እና ከአማራ ጀርባ ላይ ወርዶ ራሱን ችሎ እንዲኖር ማድረግ እኮ ለአማራ የመፍትሄዎች ሁሉ መፍትሄ ነው፡፡ እንዲህ የምንሆነው እኮ ለዩጋንዳ ወይም ለቱኒዚያ ህዝብ አይደለም፡፡ እንዲህ የምንሆነው እኮ ለአማራ ለራሱ ብለን አይደለም፡፡ እንዲህ የምንሆነው በተከዜ ማዶ አገር የተነሳ ነው፡፡
አባቶቻችን ከአጋም የተጠጋ ቁልቋል ሲያለቅስ ይኖራል አሉ፡፡ እያወቁ ግን ማለያየት ሲገባቸው የበለጠ አጠጋግተውን ሄዱ….
(ማሳሰቢያ፡- በራሱ የወራሪው ህገመንግስ አንድ የፌደራል መንግስቱ አባል መንግስት ተከፋሁ ተገፋሁ (ለአማራ በተለይ ደግሞ ተደፋሁ) ካለ መለየት መብት ነው፡፡ ስለሆነም ከላይ የተጻፈው የመብት ጥያቄ እንጅ የወንጀል ወይም የአድማ ድርጊት አይደለም፡፡)
From
https://www.facebook.com/permalink.php?story_fbid=926245850756173&id=808909555823137