Bete Amhara

Bete Amhara

Friday, June 26, 2015

አማራን አከርካሪውን ሰብረነዋል ሲሉ
------------------------------------
አማራን አጥፍቶ ትግራይን መገንባት የሚለው መርህ አርባ አመታትን ያለምንም ለውጥ ተሻግሮ እዚህ ደርሷል፡፡ የወያኔ ዋና ዋና ጸረ አማራ ቃላትም ማዳከም፤ አከርካሪውን መስበር፤ እንዳያንሰራራ አድርጎ መቅበር፤ ቅስሙን መስበር፤ ማሽመድመድ፤ ማሸማቀቅ….. ናቸው፡፡ በሁሉም ዘርፍ ለአርባ አመታት እንዲህ ነው ሲደረግብን የቆየው፡፡ አሁንማ በተለይ ብሶበታል፡፡
የአማራን አከርካሪ መስበር ብዙ ዘርፎች አሉት፡፡ የመጀመሪያው ወታደራዊ እርምጃ ነው፡፡ ወያኔ አማራ ብሎ የሚጠራውን ደርግን በወታደራዊ ጦርነት አሸንፎአል፡፡ በደርግ ሰበብም አማራ ደህና ወታደር እንዳይኖረው አደረገ፡፡ ከደርግ የተረፉትን በሰበብ አስባቡ አዳክሞ ጨረሳቸው፡፡ በራሱ ሰራዊት ውስጥ መልምሎ ያስገባቸውን አማሮች ወደላይ እንዳያድጉ የአፓርታይድ ጣሪያ ደፋባቸው፡፡ በዚህም አማራ በአገሩ ወታደራዊ መስክ የተገለለ ብሎም አከርካሪው የተሰበረ ሆነ፡፡ በፖሊስና ደህንነት ክፍልም እዲሁ፡፡ አማራ ፖለቲካዊ ደህንነት ውስጥ ድርሽ እንደማይል ይታወቃል፡፡ የማይጠቅሙም የማይጎዱም የኢኮኖሚና መሰል ደህንነት ስራዎች ብቻ ውስጥ ይሳተፋሉ--ለዛውም በጆሮ ጠቢነት ደረጃ፡፡ በዚህም አማራ ለአገሩ ጥቅም የማያበረክት እና ከአገሩም የማይጠቀም ሆነ፡፡ ወያኔ በወታደራዊ፡ ፖሊስና ደህንነት ዘርፎች ውስጥ በዚህ መልክ አማራን ከጨዋታ ውጭ አድርጎ ሁሉንም አጋፍፎ ያዘ፡፡ በዚህም አማራው አከርካሪው የተሰበረ ሆነ፡፡
በመቀጠልም ፖለቲካዊ አከርካሪ ሰበራ ውስጥ ተገባ፡፡ እንደሚታወቀው ከአማራ መካከል ተፈልገው ወደቡችልነት የሚመጡት ማሰብም ሆነ መናገር የማይችሉት ተረፈ ህዝብ ናቸው፡፡ አንድ ነገር ከወያኔ የምታደንቅለት ብትሉኝ ሆድ ተኮርና አይሞቄ አይበርዴ ሰዎችን የማግኘት ጥበቡ ነው፡፡ ወያኔዎች የሆነ ከንቱ አነፍናፊ መሳሪያ ሁሉ ያላቸው ይመስለኛል፡፡ እስኪ በቡችልነት የሚያገለግሉትን ሰዎች ልብ ብላችሁ እዩአቸው፡፡ አንድ እናት የወለደቻቸው ነውኮ የሚመስሉት፡፡ እና ወያኔ ለህዝባቸው የሚቆረቆሩትን፤ ችግርን በፍጥነት ተገንዝበው መፍትሔ የሚያበጁትን፤ የወገናቸው ፍቅር የሚያንገበግባቸውን፤ ከሆድ በላይ ህሊናና ክብር አለ ብለው የሚያስቡትን፤ እውቀትን የሚወዱትን፤ ለራሳቸው ሳይሆን ለህዝባቸው የሚኖሩትን ብርቅየ የአማራ ልጆች ወደአመራርነትም ሆነ ወደፖለቲካው መስክ ድርሽ እንዳይሉ ሌት ተቀን ይሰራል፡፡ በምትኩ በእነዚህ ድኩማን ፍጥረቶች እነዛን ብርቅየዎችን ይደቁሳቸዋል፡፡ በሌላ በኩል በተቃዋሚነት የሚንቀሳቀሱትን አማሮች የተለያየ የሽብር ክስ በመጠምጠም ያስራል፤ ያሰቃያል፤ ይገድላል፤ ያሰድዳል፤ ያሳድዳል…..በዛም አለ በዚህ አማራ ከአገሪቱ ፖለቲካዊ ህይወት ውስጥ ሰባራ አስተዋጽኦ በማያደርግበት ሁኔታ አከርካሪው ተሰብሯል፡፡ ይህም ማለት የኢትዮጵያ ፖለቲካ አማራን እዲያገል ወይም ድርሽ እንዳያደርግ ሆኖ ነው የተሰራው ማለት ነው፡፡ ወያኔ ይህንን አማራን የማግለል እና ፖለቲካዊ አከርካሪውን የመስበሩን ጥረት ቀጥሎበት ይገኛል፡፡ ባጭር ቃልም ወያኔ ፖለቲካዊ አከርካሪ ሰበራ ጦርነት ላይ ነው ያለው ማለት ነው፡፡
ወያኔ የሁሉም መሰረት የሆነውን የአማራውን የኢኮኖሚ አከርካሪ በተሳካ ሁኔታ መስበር ችሏል፤ አሁንም ይህንን ኢኮኖሚያዊ አከርካሪ ሰበራ በሀይል ተያይዞት ይገኛል፡፡ አማራን ሊጠቅሙ ይችላሉ፤ ሀብት እንዲኖረው ያስችላሉ የተባሉ ነገሮች በሙሉ ተዘመተባቸው እና በአማራ ምትክ የትግራይ ከበርቴዎች እንዲወለዱበት ሆነ፡፡ የመጀመሪያው ከወሎ እና ጎንደር ለም መሬቶችን መውሰድ ነው፡፡ እነዛ መሬቶች ለወያኔ ሁለት ጥቅም አላቸው፡፡ የትግራይን የቆዳ ስፋት በመጨመር እና ሀብቷን ማደርጀት እና በተቃራኒው አማራውን መሬቱን መሸብሸብ እና የኢኮኖሚ አቅሙን ማዳከም ናቸው፡፡ ትግራይ እየሰፋች እና እየጎለበተች በሄደች ቁጥር አማራ እያነሰና እየተዳከመ ይሄዳል፡፡ ይህም በትክክል ተግባር ላይ ውሏል፡፡ ገናም ወደፊት ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ አማራን ፈጽሞ ማጥፋት እውን እስኪሆን ድረስ….. የሰው መሬት ወስደው እንዴት በኋላ መልሱ መባላቸው ሳይታያቸው ቀረ ብላችሁ ለምታስቡ መልሱ ወዲህ ነው፡፡ ቀስ በቀስ አማራን እያዳከሙ፤ መሬቱን ደረጃ በደረጃ እየወረሩ፤ ህዝቡን በልዩ ልዩ ሰበብ እያስደዱና እየገደሉ መላ አማራን ይውጧታል፡፡ በዚህም ስኬት የድንበር ይገባኛል ጥያቄ ተደመደመ ማለት ነው፡፡ በዚህ ከቀጠለ አማራን ማጥፋቱ የጥቂት አመታት ብቻ ጥረት ስለሚሆን እንኳን ድንበሩን መሀሉን የሚጠይቃቸው የለም፡፡ እናም የሰው መሬት በየጊዜው ሲወስዱ በመጨረሻ ጠያቂ እንደማይኖራው እርግጠኞች ስለሆኑ ነው፡፡ የአምናው መሀል የዘንድሮው ድንበር፤ የዘንድሮው መሀል የከርሞው ድንበር እያለ እያለ ይቀጥልና አንድ ቀን የአሁኑ ኦሮሚያ ድንበር ይደርሳሉ፡፡ ያኔ ደግሞ ምን እንደሚገጥማቸው ወይም ምን መላ እንደሚዘይዱ አላውቅም፡፡
የዚህ አማራን በኢኮኖሚ የመስበር እርምጃ በመሬት ዘረፋ ብቻ አያቆምም፡፡ አማራን ፈጽሞ ማደህየት የሚለው ቀጣይ እርምጃ አለ፡፡ አማራ እንደሚታወቀው ምድር ላይ ካሉ ህዝቦች ቁጥር አንዱ ደሀ ነው፡፡ ይህ የተደረገው ደግሞ በወያኔ አማራን የማዳከም መርህ መሰረት ሆነ ተብሎ ስለተሰራበት ነው፡፡ የአማራ ነጋዴዎች በሰበብ አስባቡ ከውድድር ውጭ ይደረጋሉ፡፡ የተጋነነ ታክስ ይጣልባቸዋል፡፡ ገደብ የለሽ እገዛ ከሚደረግላቸው የወያኔ ነጋዴ ተብየዎች ጋር እዲወዳደሩ ይደረጋሉ፡፡ ያ ራሱ ብቻውን ድኩማን ያደርጋቸውና በመጨረሻም ከገበያ ያስወጣቸዋል፡፡ በአማራ አገርም ውስጥም ሆነ በሌላ አካባቢዎች አማራን ከጨዋታ ውጭ በማድረግ በትግሬ ባለሀብቶች እንዲያዙ አድርገዋል፤ እያደረጉም ናቸው፡፡ ዛሬ በአብዛኛው የአማራ ከተሞች እንኳን ትልልቆቹ የንግድ እንቅስቃሴዎች ትንንሾቹም በትግሬ የተያዙ ናቸው፡፡ በዚህም አማራው አከርካሪው መሰበር ብቻ ሳይሆን እግር ከወርች እደታሰረ እንገነዘባለን፡፡
በአማራ አገር የሚበቅሉ የአዝርእት አይነቶች እና እንስሳት ወደመሀል አገር ሲገቡም ሆነ ወደ ውጭ ሲላኩ በትግሬ ተማኝነት ነው እንጅ በትክክለኛ ዋጋቸው አምራቹን አማራ በሚጠቅም መንገድ አይደለም፡፡ በዚህም ስውር የሆነ የእዝ ኢኮኖሚ በአማራው ላይ እየተተገበረ እንደሆነ እንገነዘባለን፡፡ እንደሰሊጥና ጥጥ የመሳሰሉ ምርቶች በተለይ አምራቹን አማራ ሳይጠቅሙ በተመን በትግሬ ከበርቴዎች ይጋዛሉ፡፡
አማራን በእንስሳት ሀብት ማራቆት ዋናና እና እጅግ አደገኛው እርምጃ ነው፡፡ ይህ በተለይ ይዋል ይደር የማይባል ችግር እና በቻልነው ሁሉ ተረባርበን ልናስቆመው የሚገባ ነው፡፡ እንደሚታወቀው የአማራ የህይወት ምሰሶዎች መሬትና ከብት ናቸው፡፡ ይሁንና ወያኔ ገበሬውን በቀላሉ ለማስደድ እና አማራን የማጥፋት ህልሙን እንዲያፋጥንለት በሚል መነሻ ዛሬ ማንም ከሁለት ወይም ሶስት ከብቶች በላይ እንዳይኖሩት ደንግጓል፡፡ የወል የግጦሽ ቦታውችንም በመከልከል ማንኛውም ገበሬ ከብቶቹን እቤቱ አስሮ እንዲያስቀምጥ አድርገዋል፡፡ የከብቶች ቁጥር እንዲያንስ መደረግ በሚሞቱት ምትክ ያለማዋለድን መጣል፡፡ ያ ማለት ደግሞ ጥገቶች እና በሬዎች አይኖሩም ማለት ነው፡፡ የአማራ መሬት ደግሞ ያለበሬ በእንጨት ጫር ጫር ተደርጎ የሚታረስ ባለመሆኑ ገበሬው በቀጥታ ስደተኛ ነው የሚሆነው፡፡ ይህ በእውነቱ የአማራን አከርካሪ ከመስበርም ያለፈ ከባድ ችግር ነው፡፡
እንደሚታወቀው በአገሪቱ አብዛኛው ሲቪል ሰርቪስ ሰራተኛ አገልጋይ አማራ ነው፡፡ እስካሁን ሰው ሁሉ ያልተገነዘበው የሲቪል ሰርቪስ ፖሊሲ አማራን ለማደህየት ሆነ ተብሎ የታቀደ መሆኑን ነው፡፡ ሲቪል ሰርቪሱን ማሽመድመድ በቀጥታ አማራን ማሽመድመድ ማለት ነው፡፡ የሌላ ብሔረሰብ ሲቪል ሰርቪስ ሰራተኞች በጎንዮሽ መሬትም፤ ሌላም ጥቅማጥቅም እንዲያገኙ ይደረጋል፡፡ ላላደጉ ክልሎች ተብሎ የሚደረገው ማበረታቻ እና የብሔረሰብ ተዋጽኦ የሚሉት ፈሊጦች የዚህ ከአማራ ጋር ሊወቀጥ ለነበረ ሲቪል ሰርቪስ ሰራተኛ የጎንዮሽ ካሳዎች ናቸው፡፡ በብሄረሰብ ተዋጽኦ ሰበብ ብዙ የፖለቲካ ስብስብም ለሌሎች ብሔረሰቦች ስለሚሰጥ በተዘዋዋሪ የዚህ እድል ተጠቃሚዎች ናቸው፡፡ አማራ ግን እዳይኖርም እንዳይሞትም በሚያደርግ ስውር ደባ ውስጥ እንዲኖር ይደረጋል፡፡ ለዛውም ሲቀጠር በስንት አድሎ፤ በስራው ላይ ለመቆየትም ስንት መከራ እየጠበቀው፤ እየተባባረና እድገት እየተከለከለ ወዘተ ነው የሚኖረው፡፡ ዛሬ በዚህ ስውር ደባ የተነሳ ሲቪል ሰርቪስ አገልጋይ የሆነው አብዛኛው አማራ ከባርነት በማይሻል ኑሮ ውስጥ ይኖራል፡፡ ሀብት፤ መሬት፤ ቤትና ሰላም የለውም፡፡ ይህም የረቀቀ አማራን አከርካሪውን የመስበር ዘመቻ ነው፡፡ በዚህም አማራ እየሰራ የሚራብ የ“መንግስት” አገልጋይ ሆነ፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ የሚነሳው ትምህርት የሚያስገኘው ጥቅም እና ከአማራ ጋር ያለው ግንኙነት ነው፡፡
በታሪክ አጋጣሚም ይሁን በሌላ አማራው ትምህርትን የሙጥኝ ይላል፡፡ በትምህርት ዝግጅት ልክ የስራ እድልና የገቢ ከፍ ማለት የተባለው ልማዳዊ አሰራር ታዲያ አማራን ተጠቃሚ የሚያደርግ ነበር፡፡ ይሁን እንጅ አማራን ለማዳከም ባለው መሰሪ ተንኮል የተነሳ ወያኔ የትምህርትን ዋጋ ከስኳር ቸርቻሪ ባለሱቅ አሳነሰው፡፡ ይህም በረጅም ጊዜ የትምህርትን ዋጋ አፈር በማብላት ትምህርት ጠል አማራ መፍጠር እና የመጨረሻውን አማራን አደህይቶ ብቻ ሳይሆን አደንቆሮ መግዛትና ማጥፋት ለሚለው እቅዱ ማመቻቸት ነው፡፡ በዚህም አማራው በትክክል አከርካሪው ተሰብሯል ብለን እንደመድማለን፡፡
ጠቅለል ተደርጎ ሲታይ ወያኔ የተያያዘው አማራን ሞራሉን መስበር፤ ማዳከም፤ መሬቱን መንጠቅ፤ ማሰደድ፤ ማደህየት፤ ማደንቆር፤ አከርካሪውን መስበር፤ አንገቱን መቁረጥ፤ መቅበር…..ነው፡፡ በአማራ መቃብር ላይ አዲሲቷን እና ታላቋን የትግራይ ሪፑብሊክ መገንባት ነው፡፡
አንተ የኔ ወንድም--የእናቴና የአባቴ ዘር ተኛ፡ ምክንያታዊ ነኝ እያልክ እኛን ተከራከር፤ ዘረኛ አይደለሁም እያልክ አይንህን ጨፍን፤ በምትጣልልህ ኩርማን እንጀራ ተደለል፤ ከወንድሞችህ ጋር አትተባበር፤ ዳር ላይ ሆነህ ተመልከት…. ከዛም መቃብርህ ላይ ሌላ አገር ተገንብቶበት ታገኛለህ፡፡ በስጋህ ያልደነቀህ በነፍስህ ይደንቅህ ይሆን….?
ድል ለአማራ
መለክ ሐራ ከቤተ አማራ

ስለ ባህር ዳር ቴክስታይል ሰራተኞች እና ልጆች መበተን እና በአዲስ ወራሪ መያዝ

ስለ ባህር ዳር ቴክስታይል ሰራተኞች እና ልጆች መበተን እና በአዲስ ወራሪ መያዝ
_________________________________________________
መለክ እንደምን አለህ? ይህ ሳምንት አማሮች ምን ያህል ከኢኮኖሚ ውጭ እንደሆንን የምናይበት ሳምንት እንደሆነ ገልፀሃል፡፡ እኔም የማውቀውን በደል ልንገርህ፡፡ ያው መለክየ እኔ እያወራሁህ ያለሁት እስካሁንም ብቸኛ ስለሆነውና በ1953ዓ.ም ጣሊያኖች ለአያቶቻችን የደም ካሳ ይሆን ዘንድ በስጦታ ስለተከፈተው የባህር ዳር ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ የተመለከተ ነው፡፡ መለክ አብዛኛው የባህር ዳር ልጆች ወይ የቴክስታይል ያልያም የመምህር ልጆች ነን፡፡ አሁን እንዲህ ከመቀያየጣችን በፊት 75 ፐርሰንቱ የባህር ዳር ነዋሪ ወይ ቴክስታይል ይሰራል ወይ ቴክስታይል የሚሰራ ቤተሰብ አባል ነው፡፡ እኔም አንዱ ነኝ፡፡ እናልህ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ቴክስታይል ማለት የባህር ዳር ነዋሪ አዋጥቶ የገነባው የሁላችንም የግል ሃብት ይመስለኝ ነበር፡፡ ለምን መሰለኝ፡- አዎ ድሮ እኛ ሰራተኞች ልጆች የፋብሪካው ጊቢ በኛ ቁጥጥር ስር ነበር:: ከፈለግን ኳስ በፊርማ አውጥተን ከጧት እስከ ማታ የዛሬን አያድርገውና በሚያምረው የግቢው ሜዳ ላይ ያለከልካይ እንጫወት ነበር(አሁን የአሕያ ጋጣ መስሏል ምናለብት በስርዓት እንኳን ቢይዙት)፡፡ የመዋኛ ገንዳው ላይ አንዴ ቢራቢሮ ፣ አንዴ ቀዘፋ አንዴ ፣ ለንግላል (በጀርባ)፣ አንዴ … በነፃ አስፈቅደን እንዋኝበት ነበር፡፡ እናቶቻችን በሰጡን ኩፖን መዝናኛ ክበቡ ገብተን ሻይ በዳቦችንን እንቆርጥበት ነበር… በቃ ምን ልበልህ ቴክስታይል ማለት የኔ ነበር፡፡ በወቅቱ የሚገርመኝ ነገር ቢኖር ድርጅቱ ያን ያህል ሃብታም እያለ ለቤተሰቦቻችን የሚከፍለው ክፍያ ግን ድሮም ዝቅተኛ መሆኑ ነበር ፡፡ ለዛ ነው ስንቱ አዲስ ሰፈር የተሻለ የመኖርያ ሰፈር ሲሆን የኛ ነባር ቀበሌዎች በዋናነት ቀበሌ 7፣8፣9 እና 10 የደንገል ቤት ቅርስ አስመዝጋቢ ሆነን የቀረነው፡፡ የኛ ቤተሰቦች ላባቸውን ጠብ አድርገው ሰርተው በየ2 ሣምንቱ 128.00 ብር ብቻ ነብር የሚከፈላቸው፤ ያንም በደጉ ዘመን፡፡
አሁን ፋብሪካው ምን ሆነ? ከባህር ዳር ብሎም ከአማራ ህዝብ ሃብትነት ወጥቶ ለቻይና ተሸጠ ተባለ ፡፡ እውነቱ እነ ሃብቶም ፣ ጎይቶም ገቡበት፤ እስካሁን በርቀትም ቢሆን አንድ ቻይና አላየንም፡፡ ከ5000 ሰራተኛ እነሱን ጨምሮ ወደ 1300 ሰራተኛ ወረደ፤ 3700 በላይ ሰራተኞች ተባረሩ፡፡ የከተማዋ ግማሽ ህዝቦች አብረን ከህይወት መስመር ተባረርን፡፡ ሰራተኛው የት ደረሰ? ከልጂነቱ ጀምሮ ያባዘተውን ጥጥ ፀጉሩ ላይ ነስንሶ በዝቅተኛው የመንግስት ጡሮታ(ለምግብ እህል መግዣ ሳይሆን ለማስፈጫ የማይሆን ክፍያ) ይዞ ተሰናበተ፡፡ እኛ የሰራተኛው ልጆች ኳስ እንጫወትበት ከነበረ ሜዳ በዱላ ተብለን ተባረርን በርቀት ነጭ የለበሱት በፍተሻ ሲገቡ አየን፡፡ በነፃ እንዋኝበት የነበረ ገንዳ አባቶቻችን በቀን ከሚከፈላቸው ክፍያ በላይ በሆነ መግቢያ ነጭ ለባሾቹ ያላባቶቻቸው ይሞላጠፉበታል፡፡ እኛ ምን አደረግን? ሜዳውን ለመጫወቻ ስንከለከል እናቶቻችንን ቆሎ አስቆልተን ገዥ ፍለጋ መንገድ ላይ እንውላለን፡፡ መዋኛ ገንዳውን ቢነሱን አባይ ከአዞ ጋር ታግለን ሰውነታችንን ፣ ሃሞታችንን ፣ ንዴታችንን… በቀዝቃዛ ውሃ እንታጠባለን፡፡ እናቶቻችን ምን ጠየቁ? የፋብሪካው መዝናኛ ክበብ የመዋኛ ገንዳውን ጨምሮ አሁን ስሙን ረሳሁት(ምን ላድርግ በጎ ነገር ያደረጉልኝን እንዳልይዝበት ጭንቅላቴን በጠላትነት የሞሉት የዚህ ትውልድ አባል ነኝ) በአንድ ደግ ሰው ለሰራተኞች በስጦታ ከረጅም አመት በፊት የተበረከተ ነው፡፡ በነገራችን ላይ የሰውየው ሃውልቱ ግቢ ውስጥ አሁን ድረስ አለ፡፡ እና እናቶቻችን ምን ጠየቁ? የሰራተኛው መዝናኛ ክበብ ተሰጥቶን ተደራጅተን እንስራበት:: ወቅትያ ምን አለ--ይሄ ሰራተኛ ክበብ የባንዳዎቹ ልጆች የነ ዘረዓይ ነው አለ፡፡ ወይኔ አያቶቼ ……. ብሞትም አባቶቼማ አልልም ጭራሽ ከ40 አመት በላይ ያለሰው ….. ከዛስ ቤተሰቦቻችን ምን ሆኑ? ትንሽ መታከሚያ አቅም ያላቸውን አማኑኤል ሆስፒታል የሰርተፊኬት ማስረጃ ዝርዝርን ተመልከታ፡፡ ለሌሎቹ … ኧረ ይቅርብህ ይህን ሁሉ ፀበል ቤትስ አላዞርህም፡፡ ብቻ ግን አንድ ነገር ልንገርህ የያዝከው መንገድ ቀጥተኛ እና ብቸኛ አማራጭ ነው!!!!!!!!!!!! እነ ጎይቶም ምን አደረጉ; ከነሱ ጋር ተደምሮ 1300 ሰራተኛ ቀጠርን ብለው የሰው ደም እየመጠጡ 18908 ሜ2 መሬት ይዘው ይንደላቀቃሉ፡፡ የኛ አያቶች በደማቸው አስተከሉልን ፡፡ የኛ አባቶች ………………………… የባንዳዎች ልጆች …………………. እኛ ……………. ለሁሉም መለክ Google ላይ ግባና Bahir Dar Textile Mills Share Company ብለህ ሰርች አድርግ በራሳቸው የተፃፈውን ታገኛለህ
አማራ ሁሉ ወደ ጎበዝ አለቃነቱ ይመለስ!
--------------------------------------
አባቶቻችን የጎበዝ አለቃ የሚባል የመንግስትን ውድቀት ተክቶ አገር የሚያረጋጋና ወደሰላም የሚያሸጋግር አሰራር ነበራቸው፡፡ አንድ ንጉስ ሲወድቅ ወይም አካባቢያዊ ገዥዎች በጦርነትም ሆነ በሌላ መንገድ ሲወድቁ አገር እንዳትታመስ እና ህግ እንዳይፈርስ በሚል ብሂል የጎበዝ አለቃ የሚባለው አሰራር ወዲያው ተግባር ላይ ይውላል፡፡ የጎበዝ አለቃ ተብሎ የሚመረጠውም በአካባቢው ጥሩ ስምና ዝና ያለው፤ ፍትህንና ርትእን የሚያውቅ፤ ታማኝ፤ ታዛዥ፤ ጨዋ እና ጀግና የሆነ ሰው ነበር፡፡ ይህንን የሚያሟላ ሰው በአካባቢው ይመረጥና ጊዜያዊ አስተዳዳሪ ይሆናል፡፡ ህዝቡም በዛ ጎበዝ አለቃ ሀላፊነት አመራር ስር ይገባል፡፡ በዚህም አሰራር አገር አይፈርስም፤ ህግ አይጓደልም፤ ሰላም አይናጋም ነበር፡፡ ይህ የገነገነ የአማራ ስልጡን ባህል ነው፡፡ ከዚህም ጋር በተያያዘ ከ1960ዎቹ ትውልድ በፊት የነበረው አማራ በአለቃ የሚያምን ነበር፡፡ በተዋረድ የበታቹ የበላዩን ፈጽሞ እያከበረውና በትህትና እየታዘዘው የመንግስትንም ሆነ ሌላ ስራ ይሰሩ ነበር፡፡ በዚህ ዘመን በዘመናዊ ትምህርት ሰበብ የተሰበረው ያ ጨዋና ተዋረዳዊ የክብብር ስርአት በግድ መመለስ አለበት፡፡ አባቶቻችን ለቁጥር የሚታክተውን ውጫዊና ውስጣዊ ጠላት አንበርክከው እኛን ክብር ያለን ሰዎች እድንሆን ያደረጉን እርስ በእርስ በነበራቸው ጠንካራ ተዋረዳዊ መከባበር ነው፡፡ የበላዩ የበታቹን በፍጹም ትህትናና ታማኝነት ይመራል፡፡ የበታቹም በፍጹም ቅንነት፤ ትህትናና ታማኝነት ይታዘዛል፡፡ የእርሱም የበታች እንደዛው ያደርጋል፡፡ በዚህ መልኩ በስርአት ኖሩ፡፡ ያንን ስርአትም በወጉ ሳንረከብ መሀል ላይ በምእራባዊያን ትምህርት የተዋጀው ትውልድ መጣና እርስ በእርሱ ተጠፋፍቶ የአያትና የልጅ ልጅ ትስስሩን ድልድይ ሰበረው፡፡ እኛ ደግሞ የተሰበረውን መጠገን እና የተበላሸውን ማስተካከል ግዴታችን ነው፡፡ እንደዛ ስናደርግ የአማራን ባህል ወደነበረበት የስርአት ምልአት እንመልሰዋለን፡፡ አሁንም ከተደቀነብን የጥፋት አደጋ የምንተርፈውና አማራነታችንን እንዲለመልም የምናደርገው የአባቶቻችን መንገድ ከዘመናዊው ባህል ጋር አጣምረን እና አስማምተን ስንጓዝ ብቻ ነው፡፡ እርስ በእርሳችን በመመካከር ከመካከላችን ሻል ያለውን አማራ እየመረጥን የየራሳችንን ትናንሽ በጎበዝ አለቃ የሚመሩ ድርጅቶች እንፍጠር፡፡ የጎበዝ አለቃ እየመረጥን በመረጥነው የጎበዝ አለቃ አመራር መስመር እንግባ፡፡ የአባቶቻችንን መንገድ እንከተል፤ መንፈሳቸውንም እንውረስ፡፡ በዚህ መንገድ ብቻ ነው የምንድነው፡፡ ሁሉም አማራ አምስትም ሰባትም እየሆነ ጥብቅ ጓደኝነት ይመስርት፡፡ ይነጋገር፡፡ ይስማማ፡፡ ይውስን፡፡ የጎበዝ አለቃውን ይምረጥ፡፡ የጎበዝ አለቃው በፍጹም ታማኝነት እና ጀግንነት የመረጡትን ወንድምና እህቶቹን ይምራ፡፡ በጎበዝ አለቃው የሚመሩት በፍጹም ታማኛነት እና ቅንነት ለአለቃቸው ይታዘዙ፡፡ አባቶቻችን ከደረሱበት የምንደርሰው አባቶቻችን በሄዱበት መንገድ ስንሄድ ነው፡፡ አባትህ በሄደበት መንገድ ሂድ…አባትህን ሁን…..የአማራ ልጅ፡፡
ድል አማራ!
መለክ ሐራ ከቤተ አማራ
Messafint Ze Amhara
ትንሽ ስለ ጎንደር አማሮች ከኢኮኖሚ ጨዋታ ውጭነት። ከአማሮች ምድር ሁሉ ህወሓት በከፍተኛ ሁኔታ የጨፈረችበት ምድር የጎንደርን ምድር ነው ። ጎንደር ላይ መላው አማራን የሚመግብ ሃብት ነበር ። የሰጡትን የሚያበቅል ለም መሬት አለን። ህዝቧም ከመስራት ቦዝኖ አያውቅም።ሩዝ፣ ሰሊጥ ፣ጥጥ፣ ጤፍ፣ሽንብራ፣አተር ፣ኑግ፣ባቄላ፣ነጭ አዝሙድ ፣ጥቁር አዝሙድ፣ ጓያ፣በርበሬ፣ዳጉሳ፣በቆሎ፣ማሽላ፣ዘንጋዳ፣ወደሃክር፣ገብስ፣ ስንዴ ፣ዱራኛ ፣ ሽንኩርት ……በበቂ ሁኔታ ጎንደሮች ያበቅላሉ እንዲሁም ብዛት ያላቸው የቀንድ ከብቶችንም ያረባሉ።ከፍተኛ የአሳ ምርትን አለ። የማር ምርትም እንዲሁ ሞልቷል። ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኘው ገንዘብ ከዲያስፖራ የሚላከውም ወደዚች ምድር ነው።ታድያ ምን ዋጋ አለው! ይህን ሁሉ ሃብት በህወሓት የትግራይ ነጋዴዎች በየቀኑ እንዘረፋል።
ሰዎቹ ከጎንደር የሚያገኙትን ከፍተኛ መጠን ያለው ገንዘብ ጎንደር ላይ አንዲት የረባች ፋብሪካ እንኳ ሊከፍቱባት አልፈለጉም። እንደዛ ካደረጉ ህዝቡ ፋብሪካቸው ውስጥ እዬተቀጠረም ቢሆን በመጠኑ በኢኮኖሚ ማደግ ስለሚችል እንደዛ አያደርጉም። ቀን ከሌት ኢኮኖሚያችን ያለተቀናቃኝ ያልቡታል።ወተቱን ወይ ወደ ትግራይ ወይ ወደ ሌላ ቦታ ይወስዱታል። አለቀ።
የህወሓት ሰዎች ከጎንደር ገበሬዎች ከፍተኛ ሰሊጥ እና ጥጥ አምራች መሬት እንደቀሙ ይታወቃል።አሁን ሰሞኑን ደግሞ በጣም ሰፊ ለም መሬት በቋራ እና በአርማጭሆ በኩል ያለውን ለሱዳን መስጠታቸው ተረጋግጧል። ከመሬታችን ጠብታ ነገር እንኳ እንዳናገኝ ተደርገናል። አማራን ማደህየት በከፍተኛ ሁኔታ እየተሰራባት ያለች ምድር ጎንደር የመይሳው እናት ናት።
ዛሬ ደግሞ የሰማሁት ዜና እንዲህ ይላል: -
"ጎንደርን ከ ሜትሮፖሊታን ዝርዝር ለምን ተሰረዘች????????????
ጎንደርን ከሜተሮፖሊታን ከተሞች ዝርዝር ህዉሃት መሰረዙን የዉስጥ ምንጮች ገልፀዋል፡፡ ከተማዋ ከ አ/አ በመቀጠል በዝርዝሩ የተቀመጡትን መስፈቶች ለምሳሌ የህዝብ ብዛት፤ የቱሪዝም መዳረሻነትን፤ የከተማ የገቢ ምንጭን፤ ለኑሮ ተስማሚነትትና የመሳስሉትን ብታሟላም ያለምንም ምክኒያት ከሜተሮፖሊታን ዝርዝር እንድትሰረዝ ተደርጓል፡፡
ከተማዋ ከመንግስትና ከአለም አቀፍ የከተሞች ልማት ፈንድ የምታገኘዉን ገንዘብ ከመከልከሉም በላይ ከተማዋ ለምንም አይነት ኢንዱስትሪና ከተማ ልማት የቴክኒክና የገንዘብ ድጋፍ እንደማይደረግላት ታዉቋል፡፡ ከተማዋ ኢንዱስትሪ ዞን የሚባል ነገርም አይኖራትም፡፡ ከተመረጡት ከተሞች መካከል መቀሌ፤አክሱም፤ አዲስ አበባ፤ ናዝሬት፤አዳማ፤ጅማ፤አዋሳ፤በህርዳር፤ደሴና ኮምቦልቻና ንዝሬት ይገኙበታል፡፡
ይህም ሆነ ተብሎ የታቀደና ከተማዋን ለመግደል ያለመ የህዉሀት ስትራቴጅ መሆኑን ከራሳቸዉ ከፍተኛ የደህንነት ምንጮች ለመገንዘብ ችያለሁ፡፡ ……"
እንግዲህ ተመልከቱ ከአማራ ክልል በትልቅነቷ እና በንግድ እንቅስቃሴዋ አንደኛ የሆነችው ምድራችን ይህ እድል ተነፈጋት። አማራን ሲያደኸዩ እንዲህ ነው። ሁሉ ነገር ያማል!! የአማራ ልጆች በሙሉ ይህ ነገር ሊስቆጫችሁ እና እልህ ውስጥ ሊከታችሁ ፣ሊያናድዳችሁ ይገባል።
አሁንም የጎንደርን ጉዳይ እመለስበታለሁ…
<<ቤተ አማራ እና ኢትዬጵያዊነት>>
ህዝባዊ ወያኔ ሓርነት ትግራይ እንደፈለገ ከሚጫዎትባት "ኢትዬጵያ" ውስጥ አባቶቻችን የሰሯትን ኢትዬጵያ ብትፈልጓት አታገኟትም ። ያቺ ኢትዬጵያ ያለችው አማራ ሕዝብ ልብ ውስጥ ነው። የአሁኗ "ኢትዬጵያ" እየፈረጠመች ሄዴች ማለት አማራ እዬጠፋ ሄደ ማለት ነው። የጥንቷ ኢትዬጵያ አስኳል፣ የጊዬን ልጅ አማራ፣ የሌለባት ኢትዬጵያ ባዶ ቀፎ ነች። አማራ ኢትዬጵያ ውስጥ ሳይሆን ያለው ኢትዬጵያ ናት አማራ ውስጥ ያለችው። ለዛም ነው የህወሓት ሰዎች ኢትዬጵያዊነትን ለመምታት አማራን መምታት ብለው የተነሱት። እየመቱትም ያለቱ የተነሱበትን አላማ ግብ ለማድረስ ነው።
ስለዚህ ለተረዳው ሰው አማራን ማዳን፣ የምንፈልጋትን (አማራ ልብ ውስጥ ያለችውን ጊዬናዊት ኢትዬጵያን) ማዳን ማለት ነው። ኢትዬጵያዊነትን ለመምታት ኦሮሞ አልተመታም ። ትግሬ ፣ሱማሌ አልተመታም ። እርግጥ ጉራጌን የመሰሉ አንዳንድ ብሄሮች አሉ የአማራን ህዝብ ኢትዬጵያዊ ፍልስፍናን የሚያራምዱ ። በዚህም ምክንያት ነው ጉራጌ የነፍጠኞች (የአማሮች) አጋር ተብሎ በተለያዩ ዘዴዎች እዬተመታ እዬተገፋ ያለው።ህወሓት በግልፅ አማረኛ ነፍጠኛ ማለት አማሮች እና ጉራጌዎች ናቸው ብላ አስቀምጣለች
ስለዚህ አማራን አሁን ካለችው ኢትዬጵያ ገንጥሎ ለብቻው እንደ ሃገር እና እንደ ነፃ መንግስት ማቆም ማለት ኢትዬጵያን መበታተን ነው ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው።አማራን ማቆም ወደ ኢትዬጵያዊነት አስኳል መመለስ ማለት ነው። ወደ ስር መመለስ ። የማያስፈልጉ ቅርንጫፎችን መቀፍቀፍ ማለት ነው። አማራነት ውስጥ ሁሉ ነገራችን አለ። እሱን ስናተርፈው ብቻ ነው የምንድነው። እራሳችን ችለን ስንኖር የሚጎልብን አንዳች ነገር አይኖርም።የተፈጥሮ ሃብት (የእርሻ መሬት፣ታላቅ ሃይቅ፣ታላላቅ ወንዞች ፣ የከርሰ ምድር ውሃ ፣ ማእድናት ፣የተለያዩ አእዝርእት) ፣ የሰው ሃይል (የተማረ፣ገበሬ፣ነጋዴ፣ጦረኛ፣እጀ ጥበበኛ፣የኪነት ሰው) ፣ ታሪክ ፣ቋንቋ ከነ ፊደሉ ፣ሃይማኖት፣ባህል ወግ …በበቂ ሁኔታ አሉን። አማራ አባቶቻችን ኢትዬጵያዊነት ብለው ሲፈጥሩ ከሌላው ህዝብ ዘንድ ከአንድነት ውጭ የምናገኘው ጥቅም ስለነበረ አይደለም። ወደ አማራ ሃገር ከሌላው አካባቢ የሚጫንልንን ነገር ካስተዋልነው እዚህ ግባ የሚባል ነገር የለም።ለመኖር የሚያስፈልጉን መሰረታዊ ነገሮች ከራሳችን ምድር በቀላሉ የምናመርታቸው ናቸው።
ከኦሮሞው ጋር የምንኖረው ኢትዬጵያዊነትን ሲጋራን ብቻ ነው። አሁን ባለው ለወደፊቱም በሚኖረው ሁኔታ ኦሮሞ ውስጥ አማራ ፈጥሮ የጋራ እናድርጋት ያላት መተሳሰሪያችን ኢትዬጵያ የለችም አትኖርምም።እነሱ ልብ ውስጥ ያለው <<ኦሮሙማ>> ብቻ ነው። ትግራዩ ውስጥም የእኛ ኢትዮጵያ የለችም ። በአንደኛ ደረጃ ያለችው <<አደይ ትግራይ>>ስትሆን ሌላዋ ደግሞ እዬጎለበትች እንድትሄድ የምትፈለገው ፣ህወሓት እንደፈለገ የሚያሾራት ፣አማራን በየቦታው የምታፈናቅል ፣የምታርድ፣የምታንኮላሽ፣ የአማራ ልጓም የሆነችው አዲሲቷ ፀረ አማራይቱ "ኢትዬጵያ" ናት።
እናስ? እኛ እና እነሱን የምታገናኘን ኢትዬጵያ የት አለች? የለችም። ያለችው እኛ አማሮች ልብ ውስጥ ናት። ከአማራም ጋራ ነው የምትቀረው። አረንጓዴ ቢጫ ቀይዋ ሰንደቃችን (የኦሮሞ ልጆች በየቦታው የሚያቅጥሏት፣ትግራዬች ከላያቸው ገፈው ጥለው በሌላ የተኳት ) አማሮች ጋር ነው ያለችው። ያቺ አባቶቻችን ለእኩልነት ፣ ለታላቅነት ፣ለአንድነት የሰሯት በታሪክ ገናናዋ ኢትዬጵያ አሁን የለችም። የአማራ ልጅ ቁርጥህን እወቅ። ያለችው አንተ ልብ ውስጥ ብቻ ነው። አማራን መገንጠል ከሰፊዋ ግን ከልፍስፈሷ፣ ከሃይማኖት ባህል ወግ የለሿ፣ ኢትዬጵያ ወደ ጠባብዋ ግን ጠንካራዋ ፣ባለ ባህል በለ ወጓ፣ ባለ ሃይማኖተኛዋ ‪#‎ጊዬናዊት‬ኢትዬጵያ መቀየር ማለት ነው። ጠንካራ አማራን መፍጠር ። አለቀ!!
ድል ለአማራ ህዝብ!
መሳፍንት ዘ አማራ
ከ ‪#‎ቤተ‬ ‪#‎አማራ‬

Wednesday, June 17, 2015

የአማራው ኤሊትና የኤርትራ ጉዳይ


የአማራው ኤሊትና የኤርትራ ጉዳይ ኃይለገብርኤል አያሌው የቀድሞው የመዐህድ ህዝብ ግንኙነት ሃላፊ የሕብረት ም/ሊቅመንበርና የሞረሽ መስራች አባል ከፋሽስት ወረራ በሃላ በሃገራችን በፖለቲካ አጀንዳነት ያቆጠቆጠው የብሄረትኝነት እንቅስቃሴ በተለይ በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል የነበረው የኤርትራ ክፍለሃገር ከረጅም ዘመን የጣልያን ቅኝ አገዛዝ ነጻ ወጥቶ ከእናት ሃገሯ ጋር ከተቀላቀለች በሃላ የተከተለው የእንድነትና የራስገዝ አስተዳደር ጥያቄ ውስጥ ውስጡን ሲብላላ ቆይቶ የኤርትራን ነጻነት በሃይል ለማስመለስ ወድ ትጥቅ ትግል የገባው ጀብሃና ተከትሎት የተነሳው ሻአብያ የፖለቲካቸው የማዕዘን ድንጋይ የፀረ ቅኝ አገዛዝ ትግልና የፕሮፓጋንዳቸው መሰረት ባደረጉት የአማራው ሕዝብ ቅኝ ገዥነት ላይ በከፈቱት የሃሰት ጦርነት ይህ ነው የማይባል ስም ማጥፋትና ሰቆቃ መፈጸማቸው ታሪክ የማይዘነጋው ሃቅ ነው። በኤርትራ በርሃዎች የተጀመረው የአማራውን ስም የማጉደፍና የማጠልሸት ፕሮፓጋንዳ በግብታዊና ከጠባብ አመለካከት ተነስቶ የተጀመረ ማስረጃ አልባ ውንጀላ ቢሆንም ያለመታደል ሆኖ ይህው የመከነ እኩይ አስተሳሰብ እንደወረደ በመቀበል የአማራ ተወላጅ የሆኑት የዩንርስቲ ተማሪዎችን እንደ ዋለልኝ መኮንን ያሉ ጭምር በመመረዝ በቅጡ ባልተረዱት አመለካከት በጥራዝ ነጠቅነት ያስተጋቡት መፈክር ስጋና አጥንት አበጅቶ በኢትዮጽያ ብሔረተኞች እንዲፈጠሩ አጋዥ ከመሆኑም በላይ የኤርትራ ተገንጣይ ሃይሎች የዛሬውን የኢትዮጽያ ርዕሰ መንግስት ለመሆን የበቃው የትግራዩን ነጻ አውጪ ድርጅት ከአሮጌ ጠመንጃ ጋር ሱሪ አስታጥቆ በኢትዮዽያ ህልውና ላይ ሌላ የውክልና ጦርነት እንዲቀሰቀስ ማድረጉ አይዘነጋም። ሕወሐት ከሻብያም በላይ ተራምዶ የአማራውን ሕዝብ ለማጥፋትና ኢትዮጽያን የመበታተ አላማ አንግቦ በመነሳት ትግራይን ገንጥሎ መንግስት እመሰርታው በሚል የገባበት ሽፍትነት ሁኔታው ተለውጦ በእቅዱም በአላማውም ያልነበረውን ኢትዮጽያን ጠቅልሎ የመግዛት ዕድል በእኛው ስንፍናና ተላላነት በመቀዳጀቱ ይህው በመንግስትነት ሽፋን ዝርፊያና ዘረኝነትን አንግሶ ትውልዱን እያጠፋ እያሰረና እየገደለ ቀጥሏል። ሻምበል ዘውዱ የቀድሞው የመዐህድና የአርበኞች አመራር ሻብያ ወይም አሁን አለም ዓቀፍ እውቅና ያለው የኤርትራ መንግስት ለረጅም ዘመን ባካሄደው ትግል ውስጥ አንግቦት የነበረው አብዛኞቹ መፈክሮች በግዜ ሂደት ወይበው በሁኔታዎች ተጽዕኖ ተለውጠው በተፈጠረው አዲስ የሃይል አሰላለፍ ውስጥ ዋና የህልውናው ጠላት ሆኖ በተገኘው በትላንት ተላላኪው ሕወሓት ወያኔ ጋር የጌታና ሎሌነቱ ዘመን እብቅቶ በጦርነት ፍጥጫ ውስጥ በሚገኝበት በአሁኑ ወቅት በተፈጠረው የሃይል መሳሳብና ባለው ነባራዊ ሁኔታ አንጻር ተንተርሰው አዲስ የወዳጅነት ምዕራፍ የከፈቱት ኢትዮዽታዊ ሃይሎች አማራጭ የትግል ስልታችውን ገቢራዊ ለማድረግ ከኤርትራው መንግስት ጋር እያደረጉ ያለው ግንኙነት በኢትዮጽያውያን ዘንድ በድጋፍና ተቃርኖ መሃከል ሲዋዥቅ ቆይቶ በአሁኑ ወቅት በኢትዮዽያ ውስጥ ባለው ዘረኝነት የፖለቲካ እመቃና የነጻነት እጦት የሰላማዊ ትግሉን ምህዳር እጅግ ያጠበበው ከመሆንም በላይ በሰላማዊ መንገድ ለውጥ ይገኛል የሚለው ተስፋ ጭለማ የዋጠው በመሆኑ አብዛኛው ኢትዮዽያዊ በኤርትራ የተጀመረውን እንቅስቃሴ የመደገፍ አዝማሚያ እያሳየ ያለበት ወቅት ላይ ነን ። ይህን ታሪካዊና ወቅታዊ ሁኔታ እንዳነሳ ያስገደደኝ ባለፉት ወራት ወደ ኤርትራ ያቀኑትን የመዐሕድ/መኢአድ ወጣቶችን አስመልክቶ ያገባናል የሚሉ በቀድሞው የቅንጅት እንቅስቃሴ ዙሪያ የነበሩ ወገኖች ውስጥ ውስጡን በመሰባሰብ ወጣቱ እዛው ሃገር ውስጥ እንዲታገል እንጂ ወደ ኤርትራ መሄዱ ማስቆም አለብን በሚል በአዛኝ ቅቤ አንጓችነት እንቅስቃሴ የጀመሩ ሲሆን ይህ አላማቸው ከበስተጀርባው ያነገበው ተልዕኮ ምን እንደሆነ ለመረዳት ለግዜው ግልጽ ባይሆንም ፤ የትግሉ መርሆ ብለው የያዙት አቋም ያለምንም የውጭ ዕርዳታና የጎረቤት ሃገር ድጋፍ የትጥቅ ትግልን ጨምሮ ያሉትን ማናቸውንም መንገዶች በመከተል ሃገራችንን መታደግና ወያኔን ማስወገድ እንችላለን የሚል በጎ እቅድ በግራ እጃችው ይዘው ፤ በቀኝ እጃቸው ደግሞ ከኤርትራ በመነሳት የነጻነት ትግሉን እናካሂዳለን የሚሉትን ሃይሎች የሚቃወም መፈክር አንግበው ውዝግብ ለመፍጠር የሚያደርጉትን እቅድ አላስፈላጊነት ለማስረዳት ቢሞከርም ያለመቀበል ገታራ አተያይ ያለ በመሆኑ ድንገት የውዝግብ አጀንዳ ቢከፈት ሕዝባችን እንዳይደናገር ከወዲሁ ግንዛቤ ለመፍጠር ነው። እነዚሁ ወገኖች የጀመሩት እጅ እግር የሌለው የትውልዱን ሰቆቃዊ የህልውና አጣብቂኝ ያልተመረኮዘ በጭፍን ሃገር ወዳድነትና ቡድናዊ ፍላጎት ለማሳካት ውሃ የማይቋጥር ግብዝ አመለካከት ይዘው ሕዝብን ለማደራጀት መሞከር ትርጉም ያለው ውጤት እንደማያስገኝ ከወዲሁ መገመት ቢቻልም የሚያሳዝንው ግን በዚህ የዜጎች አንድነትና የተቃዋሚ ሃይሎች ትብብር ከመቼውም ግዜ በላይ በሚያስፈልግበት ወቅት ላይ ሆነን ቢያንስ በመሰረታዊ አስተሳሰብ እስከተገግባን ድረስ ታጋይ ሃይሎችን የማውገዝና የመኮነን እንቅስቃሴ ማካሄድ እንደ ትግሉ አካል አድርጎ መቁጠርና ይህንንም ለማስትናገድ መሞከር በሃገርና በትውልድ ስቃይ ላይ ነዳጅ እንደማርከፍከፍ የሚቆጠር ነው። ሌላው የትግል አጋሬ የነበረው አማራውን ለማደራጀት የደከመው የሞረሽ ወገኔ ሊቀመንበር አቶ ተክሌ የሻው ባለፈው ሰሞን በሺህ የሚቆጠር ታዳሚ በተገኘበት የኢትዮሲቪሊቲ የፓልቶክ ሩም በመገኘት ካቀረበው በሳል የታሪክ ትንተና ባሻገር ፤ በኤርትራ የተጀመረውን ትግልና ሻብያን አስመልክቶ ያለው አቋምና ያንጸባረቀው አስተሳሰብ እና ወዳጄ የምለው የእዲስ ድምጽ ሬድዮ ባለቤት አርቲስት አበበ በለው በዳላስ ያቀረበው ወቅቱን ያልመጠነ ፤ ነባራዊውን የአካባቢውን ጂኦ ፖለቲካና የሃይል አሰላለፍ ግምት ውስጥ ያላስገባ ስሜታዊና ግትር አመለካከት ፤ ሕዝባችን እየወሰደ ያለውን እርምጃ የሚጻረር ለነጻነቱ ለመፋልም ቆርጦ ሕይወቱን ለሞት አሳልፎ የሰጠውን ትውልድ መስዋዕትነት ዋጋ የሚያሳጣ ሃላፊንት የጎደለው አተያይ ተገቢና ወቅታዊ አለመሆኑን ለማስገንዘብ ነው ። አቶ ተክሌ ኤርትራንና በዛ ያለውን ትግል ጭቃ እየቀባ በሚያጣጥልበት በዚያን እለትና ሰዐት በሰላም ለመታገል ሕጋዊ በሆነ መልኩ እየታሰሩ እየተገረፉና እየተዋረዱም ቢሆን ታግሰው የተነሱለትን ሕዝባዊ አላማ ለማሳካት ደከመኝ ያላሉት የመኢአድ አባላትና አመራሮች በወያኔው የምርጫ ቦርድ ድርጅታቸውን ተቀምተው በጉልበት ከተባረሩ በዃላ የሰላሙ መንገድ ሲዝጋባቸው የአመጹን ትግል እንዲመርጡ በመገደዳችው ባለፉት ወራት ቁጥራቸው በርካታ የሆኑ ወጣቶች በቀድሞው የደርጅቱ ህዝብ ግንኙንት ሃላፊ ወጣት ተስፋሁን አለምነህ መሪነት ወደ ኤርትራ መግባታችው ዜናው እይተሰራጨ ነበር። አበበ በለው በዳላስ በኤርትራ ያለውን ትግል እያንጓጠጠ በተሳለቀብት ባለፈው ሰሞን በተቃዋሚ አባልነታችው ተጠርጥረው ከከጎንደርና ጎጃም ተይዘው መዕከላዊ የታስሩትን ወገኖች የተወለዱበት ብሔር እየተሰደበ ብልታቸ ተቀጥቅጦ መኮላሸቱን በእደባባይ በፍርድ ቤት ውስጥ ልብሳችውን እውልቅው እያሳዩ የወገን ያለህ ድረሱልን በሚሉብት በዚህ የመከራ ግዜ ቅንጡው አርቲስት ያሏለበትን ሰላማዊ ትግል ሊሰብክ እርቅና መግባባትን ሊያስትምር ሲባዝን በትዝብት ተከታትዬዋለሁ ። ለተቀማጭ ሰማይ ቅርቡ ነው እንዲሉ ፤ የፖለቲካው ትግል አልጋ በአልጋ በሆነበት ሰሜን አሜሪካ ተቀምጦ ትውልዱ አማራጭ የትግል መንደርደሪያ መሸሸጊያ አድርጎ ለወሳኙ ትግል የሚያድርገውን መነሳሳት ማንኳሰስና ትውልዱ ሊሰዋለት የወደደውን አላማ ማውገዝ አላዋቂነት ብቻ ሳይሆን ተራ ግብዝነትም ነው። ሞረሽ እንደ ሲቪክ ተቋም ሲመሰረት ካስቀመጣቸው መተክላዊ አቋሞችና የአሰራር መርሆች ውስጥ አንዱ በየትኛውም ተቃዋሚ ድርጅቶች ሕዝባዊና ማህበራዊ ተቋማት ውስጥ ያሉ የአማራና የሌላ ብሄር ተወላጅ ግለሰቦችን በመቅረብ አላማውን በማስተዋወቅ ወዳጅ የማብዛትና ጠላትን የመቀነስ ስልት በማንገብ የእርስ በርስ መጠላለፍን የሚያስወግድና የሕዝብ ለሕዝብ ግንኙነትን በማጎልበት በሕወሀት ሴራ የተበከለውን መቃቃር ለማርገብ ጥረት ማድረግ የሚችል ሃይል ለመፈጠር ነበር። እንደ አለመታድል ትልቁን ሕዝባዊ ተልዕኮ ለማሳካት የግል ስሜትን ተቆጣጥሮ ያነገቡትን እላማ ከማስቀድም ይልቅ ትንንሽ የንትርክ ሰበዞችን መምዘዝ በሚያስቀድሙ ፤ አዲሱን ትውልድ ለማድመጥ ጆሮዋችው የተደፈነና እንቆምለታለን የሚሉትን ወገን የማይወክል ፤ጥበብ የራቀውና ዲፕሎማሲያዊ አቀራረብ የተለየው ፖለቲካ በማራመድ ተለዋዋጩን የአካባቢያችንን ሁኔታ ገምግሞ ተመጣጣኝ አቋም ይዞ መገኘት በሚያስፈልግበት ወቅት በአሮጌ የታሪክ ቡሉኮ ተጀቡኖ ዘመኑን ያልዋጀ ሃሳብ ይዞ አማራን ያህል ህዝብ አደራጃሁ ብሎ ማሰብ ቀልድ መሆኑ ሊገባችው አለመቻሉ ያስዝናልም ፤ ያሳፍራልም። በአሁኑ ወቅት ከየትኛውም የኢትዮጽያ አካባቢ ካለው ወገናችን በአማራ ክልል ቁጥሩ ከፍተኛ የሆነ የወጣት ሃይል በኤርትራ ያሉትን ታጣቂ ሃይሎች በመቀላቀል ላይ ይገኛል። ከዚህ ወደ ኤርትራ በርሃ ከሚያቀኑ ወጣቶች ውስጥ ከአንዳዶቹ ጋር በሃገር ቤት በሰላማዊ እንቅስቃሴ አብረን የሰራን ከመሆኑም በላይ በሰላማዊ ትግል የቆረቡ በዚህም አቋማቸው ከወያኔ ብቻ ሳይሆን ተቃዋሚ ነን ከምንለው ጭምር ተጽዕኖ የተደረገባችው ጽናተ ብርቱ ወጣቶች ለሰላማዊ ትግሉ ማድረግ ከሚጠበቅባችው በላይ ዋጋ ቢከፍሉም ያለው አገዛዝ ሊገባው የሚችል ባለመሆኑ በሚገባው ቋንቋ ሊያናግሩት ወደ ግንባር ተንቀሳቅሰዋል ይህ በእንዲህ ባለብት ሕዝባዊ እንቢተኝነቱ እየጋመ አብዮት ያዘለ የለውጥ ዳመና ባንጃበበት በዚህ ወቅት በዉጭ በዲያስፖራ ያለነው ሕዝባዊ ትግሉ ለቅልበሳ እንዳይጋለጥ ነቅተን መገኘትና የእርስ በእርስ መጠላለፍን የሚያስወግድ ቅራኔን መፍቻ ባህል ማዳበር ይኖርብናል ። በዚህ ዘመን የተፈጠረው ትውልደ ኢትዮጽያዊ ወጣት ዜጋ በሃገሩ የኢኮኖሚ የእኩልነትና የነጻነት ማጣት እንገፍግፎት ሃገሩን ለቆ እየወጣ እየደረሰበት ያለውን ቅስም ሰባሪና እዋራጅ መከራ ጽዋው ሞልቶ እየፈሰሰ ባለበት ጭለማ ውስጥ ሕልውናው በመኖርና ባለመኖር አጣብቂኝ ውስጥ በወደቀበት የፈተና ግዜ እንደ ሞረሽና ፥ እንዳንድ የአማራው ተቆርቋሪ ነን የሚሉ ወገኖች ዘሩ እንዲጠፋ ቀን ከሌት መቃብር የሚቆፈርለትን ታላቁን የአማራ ሕዝብ እታደጋለሁ ብሎ የተነሳ ቡድን በእንዲህ ያለ ግዜ ሊረዳው የፈቀደውን የመርዳት ፍላጎት እያሳየ ያለን አንድ የጎረቤት ሃገርና መንግስት ፈቃደኝነቱን በይበልጥ እንዲያጠናክር ወደ ላቀ ደረጃ እንዲያሸጋግር ብልህነት ያለው አያያዝን መጠቀም ተገቢም አስፈላጊም መሆን ሲገባው ፤ አለያም የህዝባችንን ስሜት ግምት በማስገባትና ሞትን አምልጦ የኮበለለውን ወገን ሲባል ፤ ገለልተኛና ዲፕሎማሲያዊ ዘዴን እንደመከተል ብል የበላው የታሪክ ድሪቶ እየጎተቱ እዛ ላይ ችክ ማለት የፖለቲካ ብስለት የጎደለውና ሃላፊነትን የዘነጋ አካሄድ ነው። እንዳለመታደል ፖለቲካችን የትችትና ሂስ የማስትናገድ ባህል ስለሌለው እድገቱ እንዲገታና ባልቴታዊ የስማ በለው የአሉባልታ ባህል እንዲዳብር በማድረጉ ሠፊና ጥልቅ ማህበራዊ ጉዳት አስከትላል ። ከዚህም አንጻር የአቶ ተክሌም ሆነ የወዳጄን አበበ እና የሌሎችን ሃሳብን በነጻነት መግለጻችው ዲሞክራሲያዊ መብት በመሆኑ ባከብርም ፤ በዚህ የጭለማ ግዜ ጥያቄያችን ወርዶ ወርዶ እንደ ሕዝብ የመኖርና ያለመኖር ደረጃ አዘቅት ውስጥ በወደቀበት ሁኔታ ላይ እያለ ዳር ቆሞ መመጻደቅና ጸጉር መሰንጠቅ ተገቢ ካለመሆኑም በላይ ይህ የኔ ትውልድ የሆነው በዘመናችን ለፖለቲካ ተሳትፎ አደባባይ ብቅ ያለውና በትግሉ ሜዳ የተገኘው ወጣት በለጋ እድሜው ብልቱ እየተኮላሸ ጥፍሩ እየተነቀለ ኑሮውን በእስር እንዲያሳልፍ ተፈርዶበት ፤ በነገስው ዘረኝነት ሃገሪቷ ልትፈርስ ጠርዝ በደረስችብት በዚህ ክፉ ግዜ ሕልውናውን ለማቆየት ማንን ነው የሚጠጋው ወዴትስ ነው የሚሰደደው ፤ ሱዳን አንስቶ ያስረክበዋል ፤ የኬንያ ፖሊስ በገንዘብ ይለውጠዋል ፤ ሱማሌ ያርደናል ፤ ከቶስ በሃቅ እንነጋገር ከትባለ ከኤርትራ የተሻል መሸሸጊያ ለዚህ ትውልድ አለን? በተለይ በምዕራቡ ዓለም ተቀምጦ ሳይደራጅ የግል ዝናን ለመገንባት ጥቅሙን ለማስተጠብቅና ከጠባብ ቡድናዊ ፍላጎት በመነሳት ለራሱ የሚመቸውን እቅድና ስትራቴጂ ልቀይስ የሚለው ወገን መገንዘብ ያለበት ሃገራችን ያለችብት አደገኛ ሁኔታ ጊዜ የማይሰጥ በመሆኑ በቅንነት በጋራ ቆመን ለተሻለ ለውጥ ብንቀሳቀስ የመከራውን መነገድ እንደሚያጥር መረዳት ይኖርብናል። የጠላትን ጠላትነቱን ያለመርሳት መርሕ የለም እንጂ የሚኖር ቢሆን ኢትዮዽያችን ከጥንት እስከዛሬ ያደሟትን የቅርብና የሩቅ ጠላቶቻችንን ብንቆጥር በእርግጥ ከማን ጋር ቆመን ልንገኝ ነበር። በይቅርታ ከማልፍ ይልቅ ስንቱን አጥፍተን ስንቱን ልንቀጣ ፤ ከስንቱስ ተኳርፈን እንዘልቀው ነበር ፤ ቱርክን፤ ግብጽን ፤ እንግሊዝን፤ ጣሊያንን ፤ ሱዳንን የዚያድባሬን ሱማሌ ወዘት… የትኛውስ ሃገር ነው አፋችንን ሞልተን ወዳጅ የምንልው አልነበረም ወደፊትም አይኖርም ፥ ያለንበት ዘመን ፖለቲካ ይህን እይነት ደረቅ የስብስቴ ጊዜ አስተምህሮ የሚያስተናግድ ሳይሆን ከነአባባሉም ዘላቂ ጥቅምን እንጂ ዘላቂ ወዳጅነትም ሆነ ጠላትነት በፖለቲካው አለም የለም ። ዛሬ የሃገራችንና የህዝባችን ህልውና ጠላት የሆነው የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር በዝርፊያና ቅሚያ ራሱንና ግብረዐበሮቹ በመጥቀም አንድ ትውልድ በስደት፤ በጎዳና አዳሪነት በረሃብና ድንቁርና እንዲጠፋ ፈርዶበት በዓለም የመጨረሻው የውርደት ጠርዝ ላይ አስቀምጦን መከራችንን እያየን በምንቃትትበት ሁኔታ ውስጥ ያሉትን የጭላንጭል የተስፋ የትግል ብልጭታዎች ለማምከን ቂመኛና ቅንጡ የፖለቲካ አጀንዳ ማራገብ ተቀባይነት የለውም። ይህን ስል ችግሮች የሉም ማለት አይደልም ብዙ በማስርጃ የተደገፉ እንከኖችን በግል አውቃለሁ ፤ አሁንም በኤርትራ በርሃ የመሸጉና ከትግሉም ተለይተው ወደ ሌላ ሃገር የተሰደዱ የቀድሞ ወጣት ጓደኞቼና ልባዊ ወዳጄና የትግል አጋሬ የነበሩት በሰላማዊው ትግል ይህ ቀረሽ ተጋድሎ ያደረጉትና በሗላም ወደ በርሃ ወርደው አርበኞች ግንባርን በመቀላቀልና አመራር በመስጠት የደከሙት ጀግናው ሻንበል ዘውዱ ያሳለፉትን ውጣ ውረድ በተወሰነ ደረጃ ተገንዝቤያለሁ። ነገር ግን በኤርትራ መንግስትና በተቀረው ኢትዮጽያዊ ተቃዋሚ ሃይሎች መካከል የተዘራው ያለመተማመንን ለማስወገድ ከሁለቱም በኩል ያሉ ወገኖች የሚደረጉትን በጎ ጥረት በበቂ ያለማገዝና ፤ ከዛም በላይ በተለይ ድጋፍና ዕገዛ ከምንፈልገው ሕልውናችን ሊከስም ጠርዝ የደረሰው ኢትዮጽያዊ ወገኖች ዙሪያ የሚታይው ቅደም ተከተሉን የሳተ ፍላጎት ግልብና ሃላፊነት የጎደለው ፕሮፓጋንዳ በኤርትራ በኩል የምንልፈገውን ድጋፍ ለማግኘት ሳንካ ሊሆንብን እንደሚችል መረዳት ይኖርብናል። በዓለማችን ካሉ ሃገሮች በድህነት በችጋርና ስደት ከተዋረድነው በላይ በሃገራችን የተሻለ መጠነኛ መብትና ቢያንስ የኛ የምንለው መንግስት አጥተን ከከፋው የስደት መከራ ሃገራችን ለመመለስ እንኳ የማንችልበት ሃገር አልባዎች የሆንበት ደረጃ ደርሰን በቀን ጨለማ ተውጠን በምንቃትትብት በዚህ ክፉ ቀን በሚቻልውና በማንኛውም መንገድ ተንቀሳቅሰን ከብራችንን ማስመለስ ሲገባ የትግልና የሜዳ ምርጫ ላይ መነታረክ በሃገርና በትውልድ ላይ መቀለድ ነው። ከዚህም በላይ ለነጻነት በሚደርግው ትግል ዙሪያ ያለን የመርህ የጽናትና የትብብር ሁኔታ አለመጠናከሩና እርስ በእርሱ የሚጋጭ ሆኖ በመቆየቱ በኤርትራ ከተጀምረ የቆየው የብረት ትግል ያለ ተጨባጭ ውጤት ቢቆይም ከቅርብ ግዜ ጀምሮ ይህን ሁኔታ በመለወጥ የተሻልና ተስፋ ሰጪ እንቅስቃሴ እየጎለበተ በመምጣቱ ከአውሮፓና ከአሜሪካ ትግሉን ለመቀላቀ የተጓዙትን በሃገር ውስጥ በሰላም የመንቀሳቀስ እድል ያጡ ወጣቶች በገፍ ወደ ትጥቁ ጎራ በመትመም ለለውጥ የሚደረገውን ትግል ወደ ወሳኝ ምዕራፍ ለማሽጋገር እያደረጉ ያሉትን የመስዋትነት ሰልፍ በሞራልና በገንዘብ የመደገፍ ገዴታ ያለብን በውጭ ያለነው ወገኖች ቢያንስ መደገፍ ባንችል እንኳ ላለመስማማት ተስማምተን የሌሎችን እንቅስቃሴ ላለማደናቀፍ መሞከሩ አስተዋይነት ነው። እንደ እንድ ነጻንቱን እንደሚሻ ዜጋ ባልፉት 24 እምታት ውስጥ ለዲሞክራሲ ለዕኩልንትና ለሕዝቦች ዘላቂ ሰላምና አንድነት በሚደረገው ትግል ውስጥ ማድረግ የሚጠብቅብኝን ያህል እስተዋዕጾ አለማድረጌ ቢጸጽተኝም በ1997 ምርጫ ሕዝባዊ ድላችንን እስነጥቀን ትግሉንም ለቅልበሳ ተዳርጎ ለስደት ከበቃው በኋላ ዘውትር እረፍት የሚነሳኝ በቅንነት ሃገርና ወገንን ብለው የተሰውት በእስር ያሉት ለአስከፊ ስደት የተዳረጉት ጓዶቼ ስቃይ አንሶ ዛሬም የወግኖቼ ስቆቃ ከመቀነስ ይልቅ እየባሰ ሄዶ ሄዶ አሁን ያለንብት ወቅት ላይ ብንድርስም ፤ ይህ ግፍና መከራ ተሰምቶት ወገኑን ለመታደግ በስፋትና በጥራት ተደራጅቶ መገኘት ከነበረብት የዲያስፖራው ማህበረስብ ዘወትር አደባባይ የሚገኘው ቁጥሩ አነስተኛ ከመሆኑም በላይ ላለምስማማት የተደገመብት እስኪምስል ድርስ ማለቂያ በሌለው እጅግ ጥቃቅን ልዩነቶች ተተብትቦ ቆምኩለት የሚለውን ዓላማ በተገቢ መልኩ ከመግፋት ይልቅ በሌሎች እንቅስቃሴ ላይ ሳንካ በመፍጠር በሚፈጠርው ትርምስ ከግዜ ወደ ግዜ የዴሞክራሲው ሃይል እየሳሳ እንዲሄድ ከፍ ያለ እስተዋጽኦ ማድረጉ ሃዘናችንን ከፍ እንዲል እድርጓል ። በሃገር ቤት እንኳን የተቃዋሚ እባል ሆኖ እይደለም ከሆነ ሰው ጋር እንኳ እብሮ መታየት ዋጋ በሚያስከፍልበት የፖለቲካ ድባብ ውስጥ ጥረት የሚያድርጉትን ወግኖች ለማክበርና እውቅና ለመስጠት የምንቸገር ባለንበት ፤ በእንጻሩ እንድ ሰልፍ ላይ ያውም በስካርብና በባርኔጣ ተከልለን በመገኘታችን የምንኩራራ የዋሆች በበረከትንበት የምዕራቡ ዓለም የነጻንት ሕይውት ውስጥ እየኖርን በምን የሞራል ሚዛን ላይ ሆነን እንድሆነ በሚቸግር መልኩ በረሃ የወረዱትን የቀን ሃሩር የሌሊት ቁር መራብ መጠማትን ፤ መውደቅ መንሳትን ፤ ከዚያም በላይ መተኪያ የማይገኝለትን እንድያ ሕይውታችውን ለመስዋት ያቀርቡትን ደፋሮች የኔ ብጤው ተቃዋሚ ነኝ ባይ ባልተገራ ቃላት ማብጠልጠል ምን የሚሉት ሞራል የጎደለው የፖለቲካ ባህል ነው። እንዳርጋችውን የመሰለ የእድሜ ልክ ፖለቲከኛና ምሁር እንቦቃቅላ ሕጻናቱን ቤት እስቀምጦ በርሃ ሲወርድ ጝራና ቀኙን ሳያይ ይመስለናል ፤ ሻቢያን ሲያሞካሽና ኢሳያስን ሲያዳንቅ ያለፈ ታሪካቸውንና የወድፊት ዕቅዳችውን ሳያቅ ቅርቶ ይመስለናል ፤ አይደለም ትግሉ የሚፈልገው አቀራረብ በመሆኑ ነው። ፖለቲካ ራሱን የቻለ ጥበብ ነው ፤ ፍላጎትን ከእቅርቦት ትላንትን ሳይሆን ዛሬን ጀብደኝነትን ሳይሆን ፤ ዲፕሎማሲን ፤ ሰጥቶ መቀበልን ፤ እካባቢያዊ ሁኔታንና የሃይል አሰላለፍን ማወቅ መተንትን በስከነ ሁኔታ መመልከትን የሚጠይቅ በዕውቀትና በችሎታ የሚስራ ሙያ እንጂ የኔ ብጤ ሳይሞቅ ፈላ በስሜት እውታር የሚጀምረው ተግባር አይደልም። በእኔ እምነት የሃግራችን ችግር በጠረጼዛ ዙሪያ ሰላማዊ መፍትሄ ቢገኝ ደስተኛ ነኝ ፤ እርቅና መግባባት ተፍጥሮ ትላንትን ለታሪክ ትተን ነገን ወደ ተሻለ ቀን ለመለውጥ የሚያስች መፍትሄ ፈጣሪ ቢያድለን የዘወትር ጸሎቴ ነው ፤ ነገር ግን ቀኝህን ሲመታህ ግራህን ስጠው የሚለውን መለኮታዊ ትዕዛዝ በመፈጸም የተገኘው የሰላማዊው ትግል ውጤት ቢኖር በጥፊ ፋንታ ብልትን ማኮላሸትና ጥፍርን መንቀል ከማክብር ይልቅ መናቅ መገፋትን በመሆኑ እበው ወተት እንኳ ይሸፍታል እንዲሉ በሃገራችን ውስጥ የተንሰራፋውን ሰው በላና ፋሽስታዊ የአፓርታይድ እገዛዝ ለማስወገድ በሚቻለውና በማንኛውም መንገድ የሚካሄደውን ሁለገብ ትግል የማገዝ ሃገራዊና ወገናዊ ግዴታ ያለብን ከመሆን ጎን ለጎን የሰልጠነ የፖለቲካ ባህል ለመላበስ እንደ እርግብ የዋህ እንደ እባብ ብልህ ሁን የሚለውን የመጽሃፍ ቃል በልባችን እኑረን ሃይላችንን ሃገርንና ህዝብን ለመታድግ ላይ በማድረግ ብቅ ብቅ እያለ ያለውን የንትርክ ፋይል በግዜ ዘግተን በፈቅድንውና ያዋጣል በምንለው የትግል መስክ ለመሰማራት እግዚያብሔር ይርዳን። በመጨረሻም ላስተላልፍ የምፈልገው መልዕክት ቢኖር ሃገራችንንና ህዝባችንን ለመታደግ ግዜያችንን እውቀታችንንና ሕይውታችንን ጭምር ላቀረብን ወግኖች ያለኝን ከፍ ያለ አክብሮት እይገለጽሁ ፤ በሰላም ይሁን በሃይል ፤ ከሃገር ውስጥ ይሁን ከኤርትራ ፤ በምርጫ ይሁን በሦስተኛ አማራጭ ፤ በጸሎት ይሁን በዲፕሎማሲ ብቻ ለወገን ይበጃል በምንለው በሚቻለውና በማንኛውም መንገድ የሚደርገውን ትግል ቢቻል በመደጋገፍ ካልሆነም በመከባበር የየራሳችንን ዓላማ ለማሳካት ከመትጋት ባሻግር በማይመለከተን በሌሎች እንቅስቃሴ ውስጥ ጣልቃ ከመግባት በመቆጥብ ለትውልድና ለታሪክ የሚቆይ አሻራ ለማኖር እንድንችል በዚህ መከረኛ ትውልድ ስም አደራ ለማለት እፈልጋልሁ ።
አማራን ባህሉንም ራሱንም የማጥፋት ዘመቻ
አማራን ማጥፋት የወያኔ መርህ ነው---ተደጋግሞ እንደተባለውና በሰፊው እንደሚታወቀው፡፡ አማራ ላይ የሚደረገው ጥፋት ጀርመን በናሚቢያ ላያ ያደረገችውን ይመስላል፡፡ በቅኝ ግዛት ዘመን ጀርመን የናሚቢያን የተወሰነ ጎሳ ክፍል አንድ ላይ ሰብስቦ ጨፈጨፈ፡፡ እስከዛሬ አጽማቸው ይጎበኛል፡፡ ይህም ወያኔ አማራና ኦሮሞን ለማጋጨት በሚል ሰይጣናዊ ተልእኮ ከአንዳንድ ኦነጎች ጋር በማበር በተለያዩ ቦታዎች የጨረሳቸውን አማሮች ሁኔታ ያስታውሰናል፡፡ እንግሊዞች ቀድሞ በአውስትራሊያ ይኖሩ የነበሩ ነባር ህዝቦችን በተለያየ መንገድ አጥፍተው የራሳቸው አገር አደረጓት፡፡ በተመሳሳይ አሜሪካኖች ነባር ህዝቦችን ጨፍጭፈው አጠፉ፡፡ ስፔኖችና ፖርቱጋሎችም በደቡብ አሜሪካ ይኖሩ የነበሩ ብዙ ጎሳዎችን አጠፉ፡፡ ከትግራይ የበቀለውና ገና ከጅምሩ አማራን ካላጠፋሁ ሞቸ እገኛለሁ ያለው ወያኔ በተመሳሳይ መንገድ አማራን ማጥፋቱን ሆነ ብሎ ተያይዞታል፡፡ አማራ ካልነቃና አሁን በያዘው የማያዋጣ ኢትዮጵያዊነት ስሜት የሚቀጥል ከሆነ በቅርብ ጊዜ ውስጥ ከላይ እንደተገለጹት ህዝቦች ይጠፋል፡፡ ፈጽሞ ባይጠፋ እንኳ አናሳ እዚህ ግባ የማይባል ተጽእኖ አልባ ጎሳ ይሆናል፡፡ አንድን ህዝብ ማጥፋት ከባድ አይደለም፡፡ በጣም ቀላል ነው፡፡ ወያኔ አማራን በሚቀጥሉት 30 አመታት ውስጥ አጥፍቶ ይጨርሳል ስንል ከመሬት ተነስተን ሳይሆን በተመሳሳይ ሁኔታ የውሀ ሽታ ሆነው የቀሩ ህዝቦችን ዋቢ በማድረግ ነው፡፡ ማንም እንደጠፋው አማራም ይጠፋል፡፡ እና አሁን የገጠመን የማንነተችን የመጥፋት አደጋ ብቻ ሳይሆን ራሳችንም የመጥፋት ችግር ነው፡፡
ወያኔ ሲነሳ አንደኛ እቅዱ አማራን ማጥፋት ሲሆን ሁለተኛ እቅዱ ትግራይን ማልማት ወይም ነጻ አገር ማድረግ ነበር፡፡ ልብ በሉ፡- ትግራይ የምትመሰረተው በአማራ መቃብር እንጅ አማራ ሳይቀበር ትግራይን ማሳደግ ይቻላል አላሉም፡፡ ስለዚህ እቅዳቸው ሲጨመቅ መጀመሪያ አማራን ማጥፋት፤ ቀጥሎ ትግራይን መገንባት ነው፡፡ አማራው ያልገባው ነገር ወያኔዎች ለአማራ ያላቸው ስር የሰደደ ጥላቻ ነው፡፡ አሁንም የጥላቻቸውን መጠን ካላወቅን ቀስ በቀስ ወደተረትነት ማምራታችን እርግጥ ነው የሚሆነው፡፡
በስነልቡና ረገድ አማራ ላለፉት አርባ አመታት ከፍተኛ ዘመቻ ሲካሄድበት ነው የቆየው፡፡ የአማራን ስነልቡናዊ ዋጋ ለማጥፋት ያልተደረገ ሙከራ የለም፡፡ የበታችነት እንዲሰማው፤ በታሪክ በተደረጉ ነገሮች ጥፋተኝነት እንዲሰማው፤ አማራ ነኝ ብሎ መናገርን አሳፋሪ ነገር አድርጎ እንዲያይ ማድረግ፤ በአማራነቱ የሚደርስበትን ግፍ እነዳያይና እንዲደነዝዝ ማድረግ፤ እና የመሳሰሉት ሲፈጸሙበት ቆይተዋል፤ አሁንም ተባብሶ ቀጥሏል፡፡ ይህም ሁሉ የሚደረገው በአማራ የስነልቡና መቃብር ላይ የትግሬን የስነልቡና የበላይነት ለመገንባት ታልሞ ነው፡፡
አማራ ባለታሪክ ህዝብ እንደሆነ አለም ራስዋ ምስክር ናት፡፡ አማራ በግንባር ቀደምትነት የጥቁርን ህዝብ ታሪክ የቀየረ ነው፡፡ ጥቁር ሰው መሆኑን በጊዜው የበላይ ነን ለሚሉ ነጮች በተረገጥ ያሳየ ብቸኛው የአለማችን ጥቁር ህዝብ ነው፡፡ አማራ ታሪክ ለመስራት የተፈጠረ ህዝብ ነው፡፡ ራሱን ለማስከበር ባደረገው ተጋድሎ የአለምን ድንቅ ታሪክ በጉልህ ቀለም የጻፈ ነው፡፡ ከሞላ ጎደል የግድፈት ታሪክ የሌለው ታማኝ ህዝብ ነው፡፡ ይህ ግን አማራን ከደሙ ለሚጠላው ወያኔ የሚዋጥ አልሆነም፡፡ የአማራ የሆነን ታሪክ ሁሉ በአደባባይ ለስኳር መጠቅለያ ከማደል እስከ ቅርስ መዝረፍና ማቃጠል የዘለቀ ዘመቻ ከፍቶ ቆይቷል፡፡ የአማራን ታሪክ ማጥላላት፤ የአማራን ታሪክ ሰሪ ሰዎች ማጥላላትና መስደብ እንዲሁም ሰድቦ ለሰዳቢ መስጠት እና የተለያየ ጥላሸት መቀባት የመሳሰሉት ዋና የወያኔ ስራዎች ናቸው፡፡ ታሪኩን ምታ ጥንካሬው ይሟሽሻል የሚል ብሂል በመከተል ይህ ነው የማይባል ጉዳት አደረሱበት፡፡ የሚጨበጡና የማይጨበጡ የአማራ ታሪክ ፈርጦችን ሆነ ብለው በማጥፋት ስራ ተጠምደው መቆየታቸው የሚታወቅ ነው፡፡
አማራ የሀይማኖት ህዝብ መሆኑ በራሱ ጠላትነትን ነው ያተረፈለት፡፡ በሀይማኖት ጉዳይ ጣልቃ በመግባት ቅዱስ ቦታዎችን ከማራከስ ጀመሮ በአደባባይ በእምነት ቦታዎች ላይ መረሸን በአገራችን በጣልያን ጊዜ ብቻ የታየ ክስተት ነው፡፡ ከአረመኔም የአረመኔ ስራ ተሰራበት በአማራው ላይ፡፡ ደጀ ሰላም ላይ በጥይት ብዙ ጊዜ ተረፈረፈ፡፡ የጎንደርን እና የቅርቡን የባህርዳርን ጭፍጨፋ ዋቢ ማድረግ ይቻላል፡፡
በአጠቃላይ አማራ ላለፉት አርባ አመታት ከፍተኛ የጥፋት ዘመቻ ታውጆበት ይገኛል፡፡ ጥፋቱም እንደ ህዝብ እና እንደ ባህል ነው፡፡ አማራን ራሱን ማጥፋት እና የአማራን ባህል እንዲሁም ታሪክና ስነልቡና ማጥፋት ዋነኛ አጀንዳወች ናቸው፡፡
ወገን ንቃ ራስክን ከትፋ ታደግ---አንተ ተኝተህ ስትጠፋ ማም አይደርስልህም!
Mesafint Ze Amhara


ለአማራ ልጆች እንደማሳሰቢያ
በእውነትና በንጹህ ስሜት እናገራለሁ፡፡ ዛሬ መኖርን የከለከለን ወያኔ የበቀለው ከትግራይ እንደመሆኑ መጠን በአማራ ላይ ያላውን ጥላቻ ለመመርመር ብዙ ጣርኩ፡፡ አማራ በእውነት አብረን እንኑር አለ እንጅ ብቻየን ልኑር አላለም፡፡ ሀብት እንኳ ባይኖራችሁ ኑ አብረን እንኑር አለ እንጅ የራሳችሁ ጉዳይ አላለም፡፡ ከትግራይ አንድ ኩባያ እህል ወደአማራ አልመጣም፡፡ ምንም የተነካባቸው ነገር የለም፡፡ ሳስበው ሳስበው አማራ መልካም እንጅ ክፉ አድርጎባቸው አያውቅም፡፡ በጎው ነገር ነው ወደክፋትነት የተመነዘረው፡፡ እየሆነብን ያለውን ሳስብ ምነው ቢቀርብን፤ ምንም ላናተርፍ አገር አገር ባልን እንዲህ የምንጠበሰው ስለምንድነው እላለሁ፡፡ ቢቀርብንስ፤ ተወልደን አድገን በሰላም በራሳችን ቤት ብንኖር ምንድነው ክፋቱ እላለሁ፡፡ ህዝባችን ሳይሰደብ፤ ሳይታሰር፤ሳይሸማቀቅ፤ ሳይዘረፍ፤ ሳይዘለፍ፤ ሳይገደል በሰላም በቤቱ ውሎ ቢገባ ይሻላል፡፡ በሰላም አምልኮቱን እያከናወነ ቢኖር ይሻላል፡፡ ሰፊዋ ኢትዮጵያ ቀርታበት በሸዋ፤ በጎንደር፤ በጎጃምና በወሎ እየተንቀሳቀሰ ቢኖር ይበጃል፡፡ በሰላም መኖርን ቀላል ያደርጋል ሰው፡፡ ውሀን ከቀለብ ጤናን ከእድሜ የሚቆጥረው የለም ይላል አባቴ፡፡ አባቴ እውነትክን ነው፤ ትልቅ ኢትዮጵያ እያልን ስናልም ጭራሽ መኖርም ብርቅ ሆኖብን አረፈው፡፡ ባለንበት በሰላም መኖር ለካ ከአጉል የትልቅነት ምኞታችን በስንት ጣእሙ ይሻል ኖሮአል፡፡
ለማንኛውም ከዚህ በኋላ ማድረግ የሚገባንን ልጠቁም፡፡ ሰላማዊ ትግል ማለት ንቁ አማሮችን ለእርድ አቅራቢ ነው፡፡ በሰላማዊ ትግል ሰበብ ንቁ የሆኑ እስር ቤት ገብተው ፍዳቸውን ያያሉ፡ ይገደላሉም፡፡ እስካሁን ተመንጥረው የተያዙት የአማራ ልጆች አብዛኞች ከመንገድ ላይ የታፈሱ ሳይሆኑ በሰላማዊ ትግል ሰበብ ተመልምለው ለአራጆች የተላለፉ ናቸው፡፡ ምርጫ የሚባለው ነገር ፈጽሞ ሊሰራ የማይችል መሆኑን አለማወቅ ራሱ የዋህነት ነው፡፡ ሰላማዊ ትግል አደርጋለሁ ባዩ ነው ሞኝ እንጅ ወያኔዎች በግልጽ ተናግረዋል፡፡ በደም መስዋእት ብቻ እንደሚወርዱ፡፡ እነሱ እያካሄዱት ያሉት በዘመናዊ አለም የጥንቱን ስርወመንግስታዊ ስርአት ማራመድ ነው፡፡ አሁንም የትግራይ ስርወ መንግስት ጠባቂዎች ናቸው፡፡ የድሮው መሳፍንታዊ አገዛዝ ነው አሁን ያለው--ሌላ ነገር የለውም፡፡ ልዩነታቸው የድሮዎች በበቅሎና ፈረስ ይጓዛሉ፤ የአሁኖቹ በመኪናና አውሮፕላነ፡፡ የድሮዎቹ ጋቢና ካባ ይለብሱ ነበር፤ የአሁኖቹ ሙሉ ልብስና ዘመናዊ ጫማ ያደርጋሉ፡፡ የድሮዎቹ በጋሻና ጦር እንዲሁም በቆመህ ጠብቀኝ ይዋጉ ነበር፡ የአሁኖቹ በታንክ፡ ጀትና ሞርታር ይዋጋሉ፡፡ በዚህም የቅርጽ እንጅ የይዘት ለውጥ የላቸውም እንላለን፡፡ በይዘት የትግራይ መሳፍንት ከሆኑ ዘንዳ የሚወርዱት በሰይፍ ብቻ ነው፡፡ በምርጫ የወረደ መሳፍንታዊ አገዛዝ ታይቶም ተሰምቶም አያውቅም፡፡ ስለዚህ የአማራ ልጅ ምርጫ በሚባል መመልመያ አጋፋሪ እየገባ ሰለባ መሆን የለበትም፡፡ የቻለ መዋጋት፡፡ ያልቻለ ዝም ብሎ በሰላም መኖር፡፡
ነጻ ጋዜጣ የሚባሉትም እንዲሁ ንቁ አማራ መመልመያ እና ወደ እርድ ማቅረቢያ ሆኑ እንጅ እስካሁን ምንም አልፈየዱም፡፡ ስለዚህ በማናቸውም ሜዲያ መጸፍ የለብንም፡፡ ፌስቡክ ላይ ራሱ በእውነተኛ አካውንታችሁ በግልጽ የምትጽፉ ልጆችም ራሳችሁን ለእርድ ምልመላ እያቀረባችሁ እንደሆነ እወቁ፡፡ ድፍረትና ግልጽነታችንን እንዋጋው ዘንድ ግድ ነው፡፡ አማራ ዋና ጠላቱ ድፍረቱ መሆኑነ ማወቅ ያሻል፡፡ ከእንግዲህ ደፍረን ፊት ለፊት መናገር ራሳችንን ለእርድ ከማቅረብ በቀር አንዳች ነገር እንደማይፈይድልን እንወቅ፡፡ ለእነሱ ራሳችንን አሳልፈን አንስጥ፡፡ መፍትሔውም እባብ መሆን ነው፡፡ ምንም ሳንናገር፡ በግልጽ ሳንጽፍ፤ እና ሰላማዊ ትግል ብለን ራሳችንን ሳናጋልጥ መኖር አለብን፡፡ የሚቃወም በስውር ይቃወም፡፡ እንደእባብ እየተጥመዘመዘ የልቡን ይስራ፡፡ ይህ ያቃተው ደግሞ ዝም ይበል፡፡ በንግግራችን እና በጽሁፋችን ግልጽነት የመጥፊያ መንገዳችንን አናፋጥን፡፡ ራሳችን ለእነሱ ሰለባ አናድርግ፡፡ ድፍረት ሞኝነት እንጅ ብልሀት አይደለም፡፡ ድፍረታችንን በብልሀት ካላገዝነው ምንም ፋይዳ የለውም፡፡ ዘዴው ዝም ብሎ ራስን ሳያሳውቁ በድብቅ ስራን መስራት ነው፡፡ ድፍረት ፊት ለፊት የሚገጥምህን ልትታገልበት ትችላለህ፡፡ አጥቂህ ወያኔ ግን የሰርዶ እባብ ነው፡፡ እንደእባብ ነው በተንኮል የሚነድፍ እንጅ እንደ ጀግና ፊት ለፊት የሚገጥም አይደለም፡፡ ድፍረትህ እየገነፈለ ቢያስችግርህም አምቀህ ያዘው፤ የሚያገለግልበት ጊዜ ሲመጣ ትጠቀምበታለህ፡፡
ድል ለአማራ
Melke Hara

Tuesday, June 16, 2015

በአማራው ላይ የሚደርሰው የዘር ማጥፋት፣ የዘር ማጽዳት ይቁም። አማራዉን ከዚህ ጥቃት ለማዳን ሶስት የተለያየ ጥረቶች የተሞከሩ እና በሙከራ ላይ ያሉ ብሎ መክፈል ይቻላል።
በዘመነ ወያኔ ብዙ የአማራ ልጆች ተገለዋል፣ አካል ጉዳተኛ ሆነዋል፣ ተወልደው ካደጉበት፣ ሀብት ንብረት ካፈሩበት ቀየ እና መንደር አገራችሑ አይደለም ውጡ ተብለው ተባረዋል። ብዙ እጅግ ብዙ አማሮች የሚዘገንን ግፍ ተፈጽሞባቸዋል። በእስር ቤት ውስጥ ወንዶች የዘር ፍሬአቸውን አማራ ብቻ ስለሆኑ ይቀጠቀጣሉ፣ በግልጽ እየተነገራቸው። ትናንት በካንጋሮው የወያኔ ፍርድ ቤት አንድ ወንድማችን ሀፍረተ ስጋውን አውልቆ እያሳየ አንተ አማራ እያሉ እንደቀጠቀጡት አሳይቷል። ከዚህ በፊትም ብዙ እነዚህን የመሰሉ ነገሮችን አይተናል። ግን ሰሚ የለም፣ መስሚያቸው ተደፍኗል። አውቆ የተኛ ቢጠሩት አይሰማም። የአማራው ለቅሶ የአዞ እንባ እየሆነ ነው በወያኔ ቤት። እነ ፕሮፌሰር አስራት እንዴት በግፍ እንደተገደሉ ማስታወስ በቂ ነው። በ 2007 በተደረገው ህዝብና ቤት ቆጠራ እራሳቸው ያመኑት ነገር ነው፣ ከሁለት ሚሊዮን አማራ ጉድለት አሳይቷል። ሴቶች እንዳይወልዱ ሆን ተብሎ አማራ ክልል ብቻ የሚያመክን ክትባት ይወጋሉ። የማጅራት ገትር በሚል ክትባት ሰበብ በሚሊዮን የሚቆጠሩ ህጻናት ይገለላሉ። 
አማራዉን ከዚህ ጥቃት ለማዳን ሶስት የተለያየ ጥረቶች የተሞከሩ እና በሙከራ ላይ ያሉ ብሎ መክፈል ይቻላል። እነዚህም ባጭሩ በእኔ አረዳድ እንደሚከተለው ይቀርባሉ።
1. የመጀመሪያው ለብዙ ዘመናት አማራው እየሞተም የኢትዮጵያዊነትን ስሜት ሲያቀነቅን ነበር። በዚህ በኢትዮጵያዊነት ስሜቱ ብዙ ተሰድቧል፣ ተገሏል፣ ተፈናቅሏል፣ ብዙ መከራዎችን ተቀብሏል። ይሄንን የኢትዮጵያዊነትን እምነቱን ትምክተኛ በሚል እምነት ለማጣጣል ብዙ ጥረት ተደርጓል። 
2. ሁለተኛው ደግሞ፣ ወያኔ ባወጣው የመደራጀት መስፈርት፣ በአማራ ስም ሲደራጁ ወዲያውኑ ድርጅቶች እንዲፈርሱ ይደረጋል። ለማሳሌ መኢአድን ሌሎችም በአማራ ስም የተነሱ ብዙ ድርጅቶች ስም አጠራራቸው እንዲጠፋ ተደርጓል። እነ ሞረሽ ወገኔም መቀመጫቸውን በአብዛናው ውጭ ስላደረጉ እስካሁን አሉ።
3. ሶስተኛው በቅርቡ የአማራ ወጣቶች ቤተ አምሀራን እንመስርት የሚል አዲስ እሳቤ ይዘው ብቅ ብለዋል። በስፋትም ቤተ አምሀራ አገራቸውን ባህላቸውን እና ማንነታቸውን ለማስተዋወቅ ጥረት እያደረጉ ነው። እነዚህም ከትችት እና ከዘለፋ አላመለጡም። ብዙዎቹ በስመ አምሀራ የሚመጡ ሰዎች አብዝተው ይኮንኗቸዋል። 
አምሀራ እንደ ኢትዮጵያዊ ሲቆም ትምክተኛ እና የድርውን ስርአት ናፋቂ፤ በብሔር ልደራጅ ሲል፣ አይ አይ አማራ ብሔር ተኮር አስተሳሰብ አይገባውም እና በአንዳንዶች ዘንድ እነዚህ ስብስቦች የወያኔን አላማ ደጋፊ ይባላሉ። ሶስተኛው ተገንጥለን በተ አምሀራን የራሳችንን ማረፊያ ጎጆ እንቀልስ ሲባል፣ የማንም ለሀጫም እየተነሳ ዘረኛ፣ ጠባብ ወዘተ የሚል ስያሜ ተሰጣቸው። 
ስለዚህ አማራ ምን ይሁን? ምንስ ያድርግ?? እስኪ እናንተ ሀሳባችሑን ስጡን።

Monday, June 15, 2015

ለሁላችሁም አማራነቴን ለምትክዱ በሙሉ!
-------------------------------------------
በወገናችሁ መንገድ ቆማችሁኋል፡፡ ወግዱ፡፡ እውነት እውነት እላችኋለሁ በጣም በሀይለኛ የመከፋት ስሜት ውስጥ ነኝ፡፡ ራሳችሁ አማሮች እኔን ኦሮሞ፡ ወያኔ፡ ሻእብያ ትላላችሁ፡፡ ሞኝ ትሉኛላችሁ፡፡ አማራ አይደለህም ትሉኛላችሁ፡፡ አማራ መሆኔን እንደ ክርስቶስ ካልተሰቀልኩ አታምኑም ማለት ነው፡፡ እሽ ደግ እኔ አማራ አልሁን፡፡ ግን ከፕሮፍ. አስራት ወልደየስ በኋላ ስለእናንተ ደፍሮ የተናገረላችሁ አለ? በ20 አመት ውስጥ እረኛ እንደሌለው ተበትነን አይደለም ያለነው? ሁሉም ማንነታችንን በመካድ እና ሞታችን እንዳይሰማን አይደለም እንዴ የሚታትረው? እኔ አማራን ግደሉ አልኩ? እኔ አማራን ሰደብኩ? የሰደቡትን ተቃውሜአለሁ፡፡ የነቀፉትን ተችቻለሁ፡፡ ያዋረዱትን ረፉ ብያለሁ፡፡ ስለተገደሉብኝ ወንድምና እህቶቸ እንዲሁም እናትና አባቶቸ አልቅሻለሁ፡፡ ያ የልብ ሀዘኔ ስለ አማራ ካልሆነ የተወለድኩባት የአማራ መንደር ሰውነቴን አትቀበል፡፡ የራሴን ምቾት ለአማራ ስል አጥቻለሁ፡፡ በጣም ብዙ ጊዜ፡፡ አሁንም እንቅልፍ አጥቸ፡፡ ሰላም አጥቸ፡፡
ይህም ለአማራ ብየ የማደርገው እንጅ እንደውለታ የምቆጥረው አይደለም፡፡ ግን አማራ አይደለም መባልን ያተርፍልኛል ብየ አላሰብኩም፡፡ እኔ አማራ እንደጠላት፤ መድረሻ እንደሌው ደሀ የሚቆጠረው በስህተት ነው፡ ሃብታም ነው፡ ራሱን ይችላል ነው ያልኩት፡፡ እንደመጻተኛ ተበትኖ መድረሻ ያጣውን ወገናችንን ሰብስበን ሀብት እንኳ ብናጣ ድህነትን በሰላም ተካፍለን መኖር እንችላለን ነው ያልኩት፡፡ አማራ ለዚህች አገር አንድ ህዝብ ሊከፍል አይደልም ሊያስብ ከሚችለው በላይ አድርጓል እና እንደበጎ ስላልታየለት የራሱን ቤት ይስራ ነው ያልኩት፡፡ አማራ ዜግነት ስላጣ ዜግነቱ ይመለስለት ነው ያልኩት፡፡ አማራ አገር አልባ ስለተደረገ አገር ይኑረው ነው ያልኩት፡፡ አማራ ምድሩ ሁሉ ተሸንሽኖ ተወሰደበት፡ ተሸጠበት፡፡ እርሱም ይመለስለት ነው ያልኩት፡፡ የተካደውን ማንነቱን ለመገንባት እንዲሁም የውሸት ክህደትን ለማፍረስና ማንነታችንን ተክዶ እንዳይቀር ለማንሳት ነው እየጣርኩ ያለሁት፡፡ አማራ ጠላቱ በዝቶበታል ስለሆነም ጨርሶ ሳይጠፋ ራሱን ያትርፍ ነው ያልኩት፡፡ ለወደፊት ልጆቹ ቤት እንስራለት፡ የአባቶቻችን የዋህነት ይቁም ነው ያልኩት፡፡ አማራ አገር ለመሆን ብቃትም፡ ምክንያትም፡ ሀብትም፡ ሁሉም ነገር አለው ነው ያልኩት፡፡ የራሴን ህይወት ወደጎን ትቸ ነው እየለፋሁ ያለሁት፡፡ ለዚህ ስራየ አንዳችሁም ሻይ እንኳ አላላችሁኝም፡፡ ይህን ማሎቴ እንዴው ልፋቴን ለማሳወቅ እንጅ ከወገኔ ጉቦ ፈልጌ አይደለም፡፡ የሚናገርለት ለሌለው ወገኔ ገና ልሞትለት ነው እንኳን ይህን ማድረግ፡፡ ግን እንዴት እናንተ እኔን በዚህ ሁሉ ስራየ የአማራ ልጅነቴን ጥያቄ ውስጥ ከተታችሁት?
ለእናንተ እንደዚህ ለምታጎሳቁሉኝ ስል ሁሉንም ትቸ የራሴን ህይወት መኖር እችል ነበር፡፡ ለእናንተ ስል እንደማንም ፎቶየን እየለጣጠፍኩና አልፎ አልፎ አንበሳ ያለው ባንዴራ እያደረግኩና የስፖርት ምስል ያእደርገኩ መኖር እችል ነበር፡፡ ግን ያስተማሩኝ ወገኖቸ የሚናገርላቸው የለምና ለእነሱ መናገር አለብኝ፡፡ ከደግነት በቀር ምንም የማያውቁ ግን ጠላታቸው የበዛ ወገኖች አሉኝ እና ስለእነሱ ዝም ማለት አልሆንልህ አለኝ፡፡ ስነሱ የሚናገር ባለመኖሩ ለመናገር ቢነሳም ስለሚታፈን ያንን ለማስወገድ ነው ልፋቴ፡፡ የምታፍኑት እናንተም ናችሁ፡፡ የታፈነ ህዝብ ልጅ ነኝ፡፡ ዝም እንዳልል ህሊና አለኝ፡፡ ወገኔን ባልናገርለት ህሊናየ ይወቅሰኛል፡፡ ባጭሩ ተውኝ፡፡ አለመናገር አልችልም፡፡ የማልችለውን ነገር አድርገ ብላችሁ አታስቸግሩኝ፡፡
ግን አንድ ቀን ትክክል እንደሆንኩ ታውቃላችሁ፡፡ በዚህ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ምናልባት ትጸጸቱ ይሆናል፡፡ የኔን ያህል ስለአማራ የሚናገርላችሁ የሌላ ወገን ቢኖራችሁ ኖሮ ጠላት እንደሌላችሁ አውቅ እና መናገሬን አቆም ነበር፡፡ ግን አልመሰለኝም፡፡ የእኔን እና የጓደኞቸን ያክል የሚናገርላችሁ ቅጥረኛ ካለ እውትም የልብ ወዳጃችሁ ይበዛል ማለት ነው፡፡ ልብ ይስጣችሁ፡፡
መለክ ሐራ ከቤተ አማራ!
ድል ለቤተ አማራ!
የአገር አባት መሪ ናፈቀኝ
------------------------
የአገር አባት ናፈቀኝ፡፡ ልጆቸ የሚል መሪ አባት ናፈቀኝ፡፡ እንደ አባት ለልጆቹ የሚያስብ መሪ ናፈቀኝ፡፡ መሪ ራሱ ናፈቀኝ፡፡ መሪ በሌለው አገር መኖር እንዴት ልብን ያደማል! እንዲህ የሚል መሪ አባት ናፈቀኝ “አይዟችሁ ወገኖቸ! የተወደዳችሁ ኢትዮጵያዊያን ሆይ በያላችሁበት በኢትዮጵያ መንግስትና ህዝብ ስም ልባዊ ሰላምታየ ከዚህ ከከበረውና የህዝብ ከሆነው መንበረ መንግስት ይድረሳችሁ፡፡ ዛሬ የደረሰብንን መከራ ባሰብኩ ጊዜ ማልቀስን ሻትኩ፡፡ ግን መሪ አያለቅስም ብየ ተውኩት፡፡ ግን መሪ አባት ነውና በልጆቹ ፊት እምባን ሲያፈስ ይታይ ዘንድ አይገባም ብየ ተውኩት፡፡ ማዘንና መከፋታችሁን ባየሁ ጊዜ ከባድ ቁጣ መታኝ፡፡ ይህ የደረሰባችሁ በእኔ ዘመነ መንግስት በመሆኑ ሀዘኔ እጥፍ ድርብ ነው፡፡ ልቤ ውስጥ ድንኳን ተክያለሁ፡፡ በዚያም ድንኳን ውስጥ እስከ ቤተሰቤ ለቅሶ ተቀምጫለሁ፡፡ ዛሬ የደረሰብን ውርደት ለበለጠ ክብር ላለው ብሔራዊ ተግባር ይገፋፋንና ያበረታታን እንደሁ እንጅ ጠላቶቻችን እንዳሰቡት ፈጽሞ አንገታችንን ሊያስደፋን አይገባም፡፡ ዛሬ በስማችሁ በተሰየምኩበት ክቡር መንበር ላይ ሆኝ ቃል የምገባላችሁ ማናቸውንም አይነት መንገድ ተጠቅመን ገዳዮቻችንን የገቡበት ገብተን እንደምንበቀል ነው፡፡ አሁን የምናደርገው የበቀል እርምጃ የወደፊት እጣ ፋንታችን ላይ አላስፈላጊ ጉዳት በማያስከትል መልኩ እንዲሆን የተቻለንን ብልሀት ሁሉ እንዘይዳለን፡፡ ጠላት የጽኑ ክንዳችን ኃይል እስኪቀምስ ድረስ ፈጽሞ እንቅልፍ እንደማልተኛ አረጋግጣለሁ፡፡ በቀል የአምላካችን መሆኑን ባንረሳውም እረኛ በጎቹን በክንዱ ብርታት እንደሚጠብቅ የታወቀ ነው፡፡ ይሁንና እረኛ በጎቹን በቻለው መንገድ ሁሉ ከአውሬ መንጋጋ ቢያስጥል በአምላክ ዘንድ ያልተጠላ ነው፡፡ አሁን በዚህ ሰአት ልጆቻችሁ በግፍ የፈሰሰ ደማችንን ለመበቀል በአገራችን ስም ምለው ተነስተዋል፡፡”
ግን እንዲህ የሚል መሪ የለም፡፡ መሪ ራሱ የለም፡፡ በዚህ ስሜት ውስጥ ሆኘ፡- “ራሴ አንድ ካልሆንክ ብየ ያጉላላሁት አንሶ ያገሬን ሰው በጠላት እጅ እንዲጉላላ አልፈቅድም” ያለው አጼ ቴዎድሮስ ናፈቀኝ፡፡ “እርስ በእርስ እየተመካከራችሁ ጠላት ሳይገባባችሁ አገራችሁን ጠብቁ” ያለው አጼ ምኒልክ ናፈቀኝ፡፡ ጠላትን ገጥሞ ሚስትና እህት ቢማረኩበት እንኳ ልቡ ያልተሰበረው ንጉስ ተክለ ኃይማኖት ናፈቀኝ፡፡ “ኃይማኖት የግል ነው፡ አገር የጋራ ነው” ያለው አጼ ኃይለ ሥላሴ ናፈቀኝ፡፡ “በአንድ ኢትዮጵያዊ አምሳ ሱዳናዊ እጠይቃለሁ” ያለው መንግስቱ ናፈቀኝ፡፡ መሪ ናፈቀኝ፡፡ መሪ ናፈቀኝ፡፡ መሪ ናፈቀኝ፡፡ የህዝቡን እምባ የሚያብስ መሪ ናፈቀኝ፡፡ የህዝቤ ሞት የእኔ ሞት ነው የሚል መሪ ናፈቀኝ፡፡ የምንወደውና የሚወደን መሪ ናፈቀኝ፡፡ ውርደታችን የሚሰማው መሪ ናፈቀኝ፡፡
ከእንብላው በቀር ሌላ የማታውቁት ወያኔና ጀሌዎቹ ግን ገደል ግቡ፡፡ ክፉ እድል እናንተን እዚህ ህዝብ ትከሻ ላይ እንዳስቀመጣችሁ እወቁ፡፡ አይደለም ይህንን ታሪካዊ አገር ልትመሩ ቀርቶ ራሳችሁን አትመሩም፡፡ እናንተ በእኛ አይን ክቡራን ሳትሆኑ ክምራን ናችሁ፡፡ በክፉ ቀን የተሸከምናችሁ ሸክሞች ናችሁ፡፡ እናንተ የሆድ ቁልል ናችሁ፡፡ ዜሮ ህሊናና ጎተራ የሚያህል ሆድ ብቻ የተሸከማችሁ ክብረ ቢስ ፍጡራን ናችሁ፡፡ እናንተን በመስደቤ ከቶ አልቆጭም፡፡ ስዋረድና አንገቴን ስደፋ አልተሰማችሁምና፡፡
የወያኔ ሞት የእኛ ትንሳኤ ነው፡፡ ከወያኔ ጋር የሚቀበረው ውርደትና ማቅ ነው፡፡ ከወያኔ ሞት ጋር የሚቀበረው ለቅሶና ሀፍረት ነው፡፡ የችግራችን ሁሉ ምንጩ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ ወያኔ ለአንድ ቀን እንኳ እንዲጨፍርብን ሊፈቀድለት የማይገባ የመሀይማንና የሆዳሞች ጥርቅም ነው፡፡ ወያኔ ከመብላት በቀር ክፉና በጎ ለመለየት ያልደረሱ ድኩማን ፍጥረታት ስብስብ ነው፡፡
ወገኖቸ በርቱ!
በተለያዩ ሃገራት በኢትዮጵያዊያን ላይ በተፈጠመዉ ዘግናኝ ግድያ ንቅናቂያችን ከፍተኛ ሃዘን ተሰምቶታል፡፡
ከአማራ ዴሞክራሳዊ ሃይል ንቅናቄ የተሰጠ የሀዘን መግለጫ
በሃገራችን በተከሰተዉ ዘርፈ ብዙ ችግሮች ምክንት ዜጎቻችን በተለያዩ ሃገራት በስደት ቢኖሩም ከሃገራቸዉ የወያኔ ስርዓት የፈጠረዉን መከራ ለመሸሽ ቢሞክሩም በየደረሱበት እየተከተላቸዉ ፍፁም ዘግናኝ እና ለአሰቃቂ ግድያ ዳርጎቸዋል፡፡
ባለፉት 24 ዓመታት በሃገር ዉስጥ የወያኔ ስርዓት በበደኖ በጉራ ፈርዳ በጋምቤላ በመሳሰሉት ቦታዎች ወያኔ ኢትዮጵያዊያንን ከነነፍሳቸዉ ማቃጠሉ ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ፡፡ ይህን መከራ ለመሸሽ ያደርጉት ስደትም መፍትሄ አልሆነም፡፡
ይህን አረመኔ ስርዓት ማስወገድ ባለመቻላችን በሃገር ዉስጥም ሆነ በዉጭ ሃገራችን በታሪኳ አይታዉ የማታዉቅ ከፍተኛ የሆነ ብሄራዊ ዉርደት ገጥሞት እየተገላታች ትገኛለች፡፡ የእኛ መከራ እና ስቃይ ዕልቆ መሳፍርት እየሆነ ቀጣይነት እንዲኖረዉ ሌት ተቀን ተግቶ የሚታገለዉ የወያኔ ስርዓት እስከ አልተወገደ ድርስ አሁንም ከብሄራዊ ዉርደታችን መዉጣት አንችልም፡፡
በየመን በደቡብ አፍሪቃ በሊቢያ የደረሰብን አሰቃቂ ዉርደት ብሄራዊ ሃዘን በመቀመጥ ብቻ ልንወጣዉ አንችልም፡፡ ህልዉናችን ልናረጋግጥ የምንችለዉ እና ከብሄራዊ ዉርደት መዉጣት የምንችለዉ የወያኔን ስርዓት ብሄራዊ መነቃነቅ በመፍጠር መደምሰስ ስንችል ብቻ እና ብቻ መሆኑን ንቅናቄችን ማስገንዘብ ይወዳል፡፡
ንቅናቂችን ለደረሰብን መከራ ቀጥተኛ ተጠያቂ የወያኔን ስርዓት ያደርጋል፡፡ ለዚህም በቅርብ ቀን በተጠናከረ እና የወያኔን ስርዓት የሚያሽመደምድ አፀፋዊ እርምጃ ይወስዳል፡፡
ንቅናቄችን ለተከሰተብን ከፍተኛ ብሄራዊ ሃዘን የተሰማዉን ጥልቅ ሃዘን ለመላዉ ኢትዮጵያዊያን ይገልፃል፡፡
የአማራ ዴሞክራሳዊ ሃይል ንቅናቄ የአማራን ህዝብ ህልዉና መታደግ ኢትዮጵያን መታደግ ነዉ ብሎ በፅኑ ያምናል፡፡ ትናት በጉራፈርዳ በጋምቤላ በበደኖ ህፃናት እና ነፍሰ ጡሮች ሳይቀር በወያኔ ሲጨፈጨፉ እና በቁማቸዉ ሲቃጠሉ በወያኔ እና በጋሻ አዣግሬዎች አማራዎች ብቻ ናቸዉ በሚል ሲሳለቁብን የነበሩት ዛሬ በወያኔ መዘዝ መከራና ግፍ በተለያዩ ሃገራት እተቀበልን ያለነዉ በኢትዮጵያዊነታችን ብቻ መሆኑን ማወቅ ይገባችኋል፡፡
ለዚህ ነዉ ንቅናቂያችን ደግሞ ደጋግሞ አማራን መታደግ ኢትዮጵያን መታደግ ነዉ እያለ አጥብቆ የሚናገረዉ፡፡
ንቅናቂያችን ለዚህ ከፍተኛ ለሆነ የልብ ስብራት እና ብሄራዊ ዉርደት የዳረገንን የወያኔ ስርዓት ከምንጩ ለማድረቅ ሌት ተቀን በየበረሃዉ የሚከራተተዉ፡፡ በመሆኑም ዛሬም ነገም እስከ መጨረሻዉ የወያኔን ስርዓት ለማሰወገድ ማንኛዉንም መስዋትነት ንቅናቂያችን በመክፈል ለድል ይበቃል፡፡
በመጨረሻም ለመላዉ ኢትዮጵያዊያን መፅናናትን እንመኛለን፡፡
የአማራ ሕዝብ ትግል ያሸንፋል፡፡
የ15 አመት ህጻን እንዲህ ይቀኛል፡፡ እናንት መንዜ እናትና አባቶች አዲስ አበባ ውስጥ የወለዳችሁትን ብላቴና መንዜ አድርጋችሁ ስላሳደጋችሁልኝ አመሰግናለሁ፡፡
==============================================
ቀበቶ ፍታ
--------------
በሥልጣን ላይ ገብቶ:
ሥልጣን ከጭቁኖች መሐል ወጥቶ:
አፈር ቅሞ ያገኛትን የሹምነቱን ቀበቶ:
እንኳን ሊሰጥ ቀርቶ ፈቶ∷
ላጠለቃትም ሳስቶላት:
አስሬ ፈቶ ሲያጠብቃት∷
ያላዋቂ ሆነና…..
በክብር ያገኛትን ቀበቶ በጭሱ በላብ አጠባት፡
በርሀብ በንባ እየቀጣ ላይ ላዩን አሸበረቃት፡
ቴክኖሎጂውን አስፋፍቶ እህሉዋን ሰብሉዋን ነጠቃት፡፡
ግና ዛሬ ሕዝብ ነቃ፡
ሹመትህን መልስ አለ ቀበቶህን አውልቅ በቃ፡፡
በቃ የህዝብ ቁጣ ተነሳ፡
ውሃ የጠጣው ፈረሱ አሳተ ገሞራ አገሳ ።
አማራ በዳይ ወይስ ተበዳይ?
ብዙ ጊዜ ትግሬ ኢትዮጲያዊያኖች አልተጠቀሙም ይባላል በኔ እይታ ደግሞ ተጠቅመዋል ባይ ነኝ ያልተጠቀመ ቢኖርም በጣም አናሳ ነው ።
እነሱም ያልተጠቀሙበት ምክኒያት ይኖራል ከወያኔ ጋ ቅራኔ የገቡ እና የመቃወም አዝማሚያ ያሳዩ ይሆናሉ እንጅ ይበልጡ አልተጠቀመም የሚለው አያስማማኝም እኔ በተቃራኒው ይበልጡ ተጠቅማዋል የተጎዳው በሺ የሚቆጠር ነው ባይ ነኝ።
ለዚህም ብዙ ምሳሌ አለኝ በዝች በኔ እድሜ ልብ ካወኩ ጀምሮ ብዙ ነገሮችን አይቻለው ነገር ግን እየቆየ ነው የገባኝ በጊዜው በመጥፎ አላየውትም ነበር።
ከተዘብኩት ነገር ላካፋላችሁ ወደድኩ እኔ በተማርኩበት ትምህርት ቤት በ ሰሜን ጎንደር ደባርቅ ከተማ የ ሃይስኩል ተማሪ ሆኘ ከ አሰተማሪወቻችን 80 በ 100 የትግራይ ተወላጆች ነበሩ ለትውስታ ያክል እኔን ካስተማሩኝ ትንሽ አስተማሪወች ጠቀስ ላድርግ ከኔ ጋ የተማራችሁ በደንብ ታቃላችሁ ።
ጎይቶም፣ ፍስሃ ፣ተስፋይ ፣ሃጎስ እና ገ/ኪዳን ነበሩ የረሳዋቸሁም አሉ ከ6 አመት በሃላ ላይ ሆኘ ስለሆነ እማወራ የማስታወስ አቅሙ ብዙ አይደለም ነገር ግን የነበራቸው የዘረኝነት በሽታ እና ከተማሪው ጋ አለመግባባት የማይዘነጋ ትውስታ ነው በተለይ መምህር ፍስሃ ኬሚስትሪ መምህሬ ሲሆን አማረኛ ግን አይችልም።
በ ፕላዝማ ነበር የምንማረው መቸም እንደኔ ያሉ እንግሊዘኛ የሚነስራቸው ጉዋደኞቸ በ አማረኛ ኢንዲተረጎምልን እንፈልግ ነበር ነገር ግን ፍስስሃ ደግሞ እኛን እንግሊዘኛ እንደሚነስረን ሁሉ እሱን አማረኛ ይነስረዋል ታዲያ በ 5ኛው ክፍለ ጊዜ እሱ ሊገባ ሲል ከሚከታተሉት ጠ ረጴዛ ተደግፈን እምናንቀላፋው እንበዛለን።
መቸም ፍሴ ደደብ እምትለውን ስድብ ሳያዛንፍ ነው እሚጠራት ደደብ እያለ ከትጋደምንበት ጠርጴዛ ቾክ ወርውሮ ጭንቅላታችን ቀጭ ማድረግ የሱ የዘወትር ቁርሾ ናት።
እናም ፍስሃም ሆነ ሌሎቹ ወደ ማታ አካባቢ ከ ወክም ሆነ ከሚካኤል ቤተክርስቲያን ከ አውደምህረት ትምህርት በኃላ የሚሰበሰቡባት አንዲት ባርናሬስቶራት ነች ያችም በ መዘጋጃ ቤቱ ጀረባ ወደ መዳህኒያለም ቤቴክርስቲያን መንገድ የምትገኘው የነ አቶ በርሄ ባር ነች።
መቸም ከሌላ ሰው ምሽት ቤትም ይሁን ሆቴል ይገባሉ ማለት መሽቶ አይነጋም ማለት ነው አቶ በርሄ ባርና ሬስቶራንት ብቻ ሳይሆን ሱቅም አላቸው አሁን ደግሞ ኢንተርኔት ቤትም ከፍተዋል ታዲያ የበርሄ የንግድ ቦታወች በ እነዚህ መምህራን ነው እምትከበበው ማለት ይቻላል ሁሌም ማታ ማታ ከዛች አካባቢ እነ ጎይቶምን ማየት አዲስ አደለም በዚህ የተነሳ የነ ብርሄን ሰፈር ትንሽዋ ውቅሮ የሚሉት ልጆች ነበሩ ።
አንዳንዶቹ ደግሞ አድዋ ሰፈር ይልዋታል ግን የሰፈሩ ሰው እና የአካባቢው ተወላጅ ፍቅር ነስቶቸው አያቅም ማንም ይህም አያስተውሎም የተወሰነው ነን እንጅ ብዙ የ ደባርቅ ሰው ግድ የለውም አንድ ነን ብሎ ያስባል እነሱ ግን አንድ ነን ብለው ቢያስቡ ክህብረተሰቡ ጋ ይቀላቀሉ ነበር ብዙ ጊዜ የማያቸው ካንድ ቤት ሙልት ብለው ስለሆነ ይገርመኝ ነበር።
ታዲያ ይህን የመሰለ የ አማራ ህዝብ በላይ ሆኖ አማራ ጨቁዋኝ ህዝብ ነው ማለት አይከብድም??
የዛው የሃገሩ ተወላጆች ተምረው ተመርቀው ለረዥም አመታት ያለስራ ይቀመጣሉ ግማሺቹ ይሰደዳል ግማሾቹ ድግሪ ይዘው ገጠር ቆላ እና በርሃ ለስራ ይላካሉ
ከ ትግራይ የመጡት ግን ቅብርር ብለው ከተማ ውስጥ እንደፈለጉ ያስተምራሉ ግምገማ የለባቸው ምን የለባቸው
ታዲያ ማነው ጨቁዋኝ አማራው ወይስ ከ ትግራይ የመጡት?
ፍርዱን ለናንተ ትቸዋለው።
በጌ ምድርማ አማራነት ብቻ ሳይሆን እስራኤልነትም አለበት!
===========================================
አንድ ወለፈንዲ ወያኔ ከነ ጭፍሮቹ ሰሞኑን በጌምድር አማራ አይደለም፤ አንድ አረማዊ የወንድ ብልት አምላኪ የአክሱም ንጉስ ከሜርዌና ኑብያ ማርኮ አምጥቶ ያሰፈራቸው ሱዳኖች ናቸው ብሎ ለያዥ ለገናዥ አስቸግሮ ሰንብቷል፡፡ ደጋግመን እንዳልነው ወያኔ ጎንደርን ከከጀላት ከራርሟል፡፡ አማራን አዳክሞ፤ ከፋፍሎ እና ገድሎ ማጥፋት በሚለው ዋናው አጀንዳቸው ስር የሚገኘው ያልተጻፈው እቅድ አንድ ጎንደርን ትግራይ ማድረግ ነው፡፡ ጎንደርን ትግራይ የሚያደርጓትም ህዝቡን ዘሩን በማጥፋት አንዱ መንገድ ነው፡፡ በወልቃይትና ጠገዴ እንዳደረጉት እና እያደረጉት እንዳለው፡፡ ሁለተኛው ጎንደርን አማራነቱን መግፈፍ ነው፡፡ ይሄው ከሰሞኑ ቅማንትን ከሰሞኑ እንደግራምጣ ሰንጥቀው በማውጣት እንዳሳዩት ማለት ነው፡፡ ከዚህም የተረፈውን አማራ አይደለም ገሌ መሌ በማለት ማንነቱን ማጥፋትና ብሎም በተለያዩ ስውር ደባዎች አመናምኖ መጨረስ ነው፡፡
የዚህም እርምጃ መጨረሻው ላይ የደረሱ የመስላሉ፡፡ ጎንደርን ለመዋጥ ከመቸውም በከፋ ሁኔታ መንጋጋቸውን እያፋጩ ናቸው፡፡ ቤተ አማራም ቀድሞ መንቃቱ የጥርስ ግጭት ፍጭታቸውን አቅሉን የሳተና የተወነጋገረ አድርጎታል፡፡ ሲሻቸው ጎንደርና ትግሬ አንድ ነው ይላሉ፡፡ የዚህ ንግግግ አላማ ግልጽ ነው፡፡ ጎንደርን ከሌላው ቤተ አማራ ነጥሎ ለማጥቃት እንዲመቻቸው ነው፡፡ በል ሲላቸው ወልቃይት የሚባል ልዩ ህዝብ እንዳለ ያስመስሉና ዘሩን ማጥፋታቸውን ቤተ አማራ አይመለከተውም አይነት ወሬ ያናፍሳሉ፡፡ ቁጣቸው ሲገነፍልም ሱዳን፤ ምርኮኛ ምናን ይላሉ፡፡ ሲከፋም እኛ ሴማዊ ነን ደማችን ንጹህ ነው፡፡ በጌምድርም ሆነ መላው ቤተ አማራ ንጹህ ደም የሌለው ኩሽ ነው ይላሉ፡፡ ግን ከነዚህ ጋር እስካሁን የኖርነውን ዘመን ሳስበው በጣም ያበሽቀኛል፡፡ አብረን መኖር ከማይገባን ህዝብ ጋር ነው በስህተት የኖርነው፡፡ በጣም ያሳዝናል ነገሩ፡፡ እነሱ እንግዲህ ከነሱ ውጭ ላለው ህዝብ ያላቸው አመለካከት እንዲህ ነው፡፡ ለዛም ነው ልንግባባ ያልቻልነው፡፡ ለዚህም ነው ሲያርዱን እና ሲገድሉን ምንም የማይሰማቸው፤ ለዚህም ነው ሰው እንደገደሉ የማይሰማቸው፡፡ ከሀሳባቸው እንደተረዳነው እነርሱ ሰው ሳይሆን እየገደሉ ያሉት ኩሽ የሆነና ንጹህ ደም የሌለው ፍጥረት ነው፡፡
የነሱ የደም ጥራት የቤተ አማራ መሳቂያ መሳለቂያ ከመሆን የዘለለ ትርጉም እንደሌለው አውቃለሁ፡፡ ነገር ግን አካፋን አካፋ ካላሉት የውርቅ ማንኪያ ነኝ ይላል በሚለው ብሂል መሰረት በልካቸውና በወርዳቸው ልክ መልስ ልሰጣቸው ወድጃለሁ፡፡ ከእንግዲህ ኢትዮጵያ እንዳትፈርስ፤ አገር እንዳይበተን ምናምን እየተባለ ዝም ስንል የኖርንበት ዘመን አልፏል፡፡ ኢትዮጵያ የአማራ ሸክላ ናት፡፡ ስለሸክላችን ከምንሞት ሸክላችንን እኛው እንቦጭ አድርገን ሰብረናት ራሳችንን ብናተርፍ ይሻላል፡፡ አማራ የራሱን ሸክላ ቢሰራም ቢሰብርም መብት እንዳለውም ይወቁ፡፡ በራሳችን ሸክላ ባለቤቶቹም አድራጊ ፈጣሪዎቹም እኛው ነን፡፡ እኛም ከእንግዲህ ልባችን እውነቱን እያወቀው ለአገር አንድነት ሲባል ሆድ ይፍጀው ብለን የያዝነውን ሁሉ አውጥተን ማፍረጥና ማንነታችንን ማሳየት አለብን፡፡ ከእንግዲህ እነሱ አንድ እርምጃ ሲራመዱ እኛ አስር እርምጃ እንራመዳለን፡፡ በጥፊ የመታንን በጎመድ እናዳሻለን፡፡ ማንነታችንን ሊክድ ለተነሳ የራሱን ማንነት እንዲክድ ወይም እንዲጠላው አድርገን እናፈርሰዋለን፡፡ ምክንያቱም ቤተ አማራ ልወርውር ካለ ሁሉም የሚወረወሩ እውነቶች አሉትና፡፡ በውሸት የተካበን ስድባችንን በእውነት ጠጠር ብቻ እናፈርሰዋለን፡፡
እናም በጌምድር እነሱ እንደሚጠቅሱት የአንድ ወለፈንዴ ፈረንጅ ጽሁፍ አለመሆኑን አበክሬ ነግሪያቸዋለሁ፡፡ የሰው ሀሳብ ፈጽሞ የማይገባቸው ፍጥረቶች ቢሆኑም ቅሉ፡፡ የሰጣኋቸው መልስም በጌ ምድር በትንሹ የሚታወቁ ሶስት መላምቶች ይሰነዘሩበታል፡፡ በጌ ምድር ማለትም የበግ አርቢ አገር ማለት የሚለው አንዱ ነው፡፡ ይህንንም ነባራዊ ሁኔታውን በማየት ሊያስኬድ የሚችል እንደሆነ እንገነዘባለን፡፡ አብዛኛው የቤተ አማራ ክፍል ደጋና ወይና ደጋማ ለበግ እርባታ ምቹ የሆነ ነው፡፡ ምንጃር የጤፍ አገር እንደምንለው ቤተ አማራ የበግ አገር የሚል አንድምታ ይሰጣል፡፡ ሁለተኛው መላምት አንድ ንጉስ (ስሙን ዘንግቸዋለሁ) አፈረ ዋናት (የዛሬው ባህርዳር እስከ ፎገራ መለስ ጎንደርና ስሜንን ያጠቃለለ) ዋና ከተማ ላይ ከተሞ ነበር፡፡ ከዛ በፊት ባደረገው ጦርነት ማሸነፉን ለማስታወስ በጄ ምድር (ምድር በእጀ ሆነች) ማለቱ ተዘግቧል፡፡ (ለዚህ ምንጭ ቤተ እስራኤል በኢትዮጵያ የምትል ትንሽ መጽሀፍ እንዳነበብኩ አስታውሳለሁ)፡፡ እናም በዚህ መላምት በጌ ምድር ማለት ምድር በእጀ የሚል ንጉሳዊ ቃል ነው፡፡ ሶስተኛው ቤጃ የሚባል ህዝብ ይኖርበት ስለነበር ከዚሁ ህዝብ ስም የመነጨ ስያሜ ነው የሚለው ነው፡፡ በተለይ ይህ ሶስተኛው መላ ምት አያስኬድም፡፡ ምክነያቱም መቸና ከየት እስከየት ለሚሉት ጥያቄዎች ምንም አይነት መልስ የሌለው በመሆኑ፡፡
ወለፈንዴ ወያኔዎች ያመጡት የዚህ የሶስተኛው መላምት ተያያዥነት ያለው አራተኛ መላምት ደግሞ ጎንደር ወይም የድሮው በጌ ምድር አንድ የአክሱም ንጉስ ከሱዳን ሜርዌና ኑብያ ማርኮ ያመጣቸው 12 ሰውች ነበሩ መጀመሪያ የሰፈሩት የሚል ነው፡፡ ይህ እውነት ቢሆን በጣም ደስ የሚል እድል ነው በእውነቱ፡፡ ምክንያቱም ሜርዌና ኑብያ በጣም ስልጡን ህዝቦች ነበሩና፡፡ ዘላን የሆነው ቅድመ ክርስትና የአክሰም ንጉስ እንዳጠፋቸው ይታወቃል፡፡ ይህም የዚህን የወያኔዎችን አካባቢ ህዝብ ከጥንት ጀምሮ የኖረ ጸረ ስልጣኔ ባህርይ የሚያሳይ ነው፡፡ ከዛ አካባቢ የሚመነጩ ኤሊቶች ሁልጊዜም የኢትዮጵያን ስልጣኔ አውዳሚነታቸው ከዛ የሚመነጭ በሽታ ይመስላል፡፡ ለምሳሌ በጎንደር መንግስትን ጥለው እንዴት አገር መምራት እንዳለባቸው ምንም እውቀቱ ስላልነበራቸው ዘመነ መሳፍንትን ማምጣታቸው፤ በአጼ ቴዎድሮስ የተጀመረውን የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ አብዮት የውጭ ጠላት መርተው በማምጣት ማጨናገፋቸው፤ በጠብ መንጃና መጋረጃ በመታለል ለውጭ ጠላት በር እየከፈቱ በየዘመኑ ማስገባታቸው፤ አሁን አለም የት በደረሰበት ጊዜ ኢትዮጵያን ከእንስሳ በሚያንስ ለሰው ልጅ ስልጣኔ ፍጹም ስድብ የሆነ ስርአት ውስጥ መክተታቸው እና ሌሎቹም ጸረ ስልጣኔ ባህልና ባህርያቸውን ያሳያል፡፡ በጠቅላላው የጎሳዊ ስሜት በስልጣኔ ኋላ መቅረትን የሚያመለክት ነው፡፡ ዛሬም ስልጡን ከሆነው ምክንያታዊ የሰው ልጅ ባህርይ ይልቅ ለስሜታዊ ህላዌ በማድላታቸው የዚህ ያለመስልጠን ባህርይ ሰለባዎች እንደሆኑ ማረጋገጫ ነው፡፡ እናም ይህ የምርኮኛ ቲዎሪያቸው ትክክል ከሆነ ቀድሞም ስልጣኔያችንን ያጠፉት እነሱ መሆናቸውን ያረጋግጣልናል፡፡ እጅግ ስልጡን ከሆኑት ዘሮች መምጣታችንም ያኮራናል፡፡ አልገባቸውም እንጅ እነዛ ቤተ አማራን ለመስደብ የጠሯቸው የዛሬዎቹ ሱዳኖች የግብጽ ስልጣኔ ባለቤቶች ናቸው፡፡
ስለነሱ ረብ የለሽ መላምት ይሁንን ካልኩ ዘንዳ አንድ የሚጎረብጣቸውን እውነት ልሰንግላቸው፡፡ መቸም ቤተ አማራ የአይሁድ ደም አለብን ብንል በትህትና የምንናገረው እንጅ የምንመካበት አይደለም፡፡ ተመክተንበትም አናውቅም፡፡ ለክርስትናችን ስንል ደብቀን ያስቀመጥነው ነገር ግን በጣም እውነት የሆነው ነገር በደማችን ውስጥ የእስራኤላዊያ ደም መኖሩን ነው፡፡ ቤተ አማራ ከጥንት ጀምሮ ከእስራኤላዊያን ጋር ጥብቅ ግንኙነት ነበረው፡፡ በተለያዩ መዛግብት እንደሚገለጸው እስራኤላዊያን በቤተ አማራ ምድር ሁሉ በስፋት ነበሩ፡፡ በኋላ ሀይማኖታቸውን ወደክርስትና እስከቀየሩበት ጊዜ ድረስ፡፡ ይልማ ደሬሳ በጻፈው የኢትዮጵያ ታሪክ በ16ኛው ክፍለ ዘመን ከሚለው መጽሀፍ ውስጥ በጌምድር ላይ በተለይም ስሜን ላይ ቤተ እስራኤላዊያን መንግስት መስርተው እንደነበር ይገልጻል፡፡ ያም መንግስታቸው በአጼ አምደ ጽዮን ተደመሰሰባቸው፤ እነርሱም ወደክርስትና እምነት እንዲቀየሩ ሆነ፡፡ ከታች ከጠቀስኩት መጽሀፍ ደግሞ ቀድሞ በ6ኘው ክፍለዘመን በዚሁ አካባቢ መንግስት መስርተው እንደነበር ይተርካል፡፡ የዮዲትንም ሁኔታ ማወቅ ያሻል፡፡ አይሁዳዊት ነው ትክክለኛ ስሟ፡፡ እርሷም የቤተ እስራኤሎች ንግስት ነበረች፡፡ ይህ በዘጠነኛው መቶ ክፍለ ዘመን ነው፡፡ እና ቤተ አማራ አብዛኛው በሀይልም በውድም ወደክርስቲያን የተቀየረ ህዝብ ነው፡፡ በደሙም ውስጥ የእስራኤላዊያ ደም አለበት፡፡ ይህንን የምለው እውነትን ስለመናገር እና ወለፈንዴዎችን ስለማሳፈር እንጅ በእውነት አማራነታችንን ለማረጋገጥ ማዶ መሻገር አስፈላጊ ሆኖ አይደለም፡፡ አማራነታችን ከበቂም በላይ እንደሆነ ሁላችንም እናውቀዋለን፡፡ የሩቅም የቅርብም ጎሮሮውን ይተናነቀው እንጅ ሀቋን ያውቃታል፡፡ መጀመሪያ እንደጠቀስኳት መጽሀፍ ቤተ እስራኤሎች ነበሩበት የተባሉት ቦታዎች ሁሉም (ከሽሬ በቀር) ቤተ አማራ ውስጥ ናቸው፡፡ እንዴውም ያንን ያየ ቤተ አማራ በሙሉ ለማለት በሚያስችል ሁኔታ እስራኤላዊያን ሰፍረውበት እንደሆነ ይረዳል፡፡ ይህም የቤተ አማራን እና የእስራኤላዊያንን መቀላቀል የሚያስረዳ ነው፡፡
ከዚህም በመነሳት ይመስላል የሀይማኖት አባቶች እኛ እስራኤል ዘነፍስ ነን፤ እነዛኞቹ እስራኤላዊያን እስራኤል ዘስጋ ናቸው የሚሉት፡፡ ይህንም ሲሉ እኛ ክርስትያን ሆነናል፡፡ ስለዚህ በነፍስ እስራኤል ነን፡፡ ይላሉ፡፡ የነብዩን ኤርምያስን “እናንተስ እስራኤላዊያ ለእኔ እንደ ኢትዮጵያዊያን አይደላችሁምን” የሚለውንም ከዚህ ጋር ማያያዝ ይቻላል፡፡ ኢትዮጵያ ሲል በአመዛኙ ቤተ አማራ ማለቱ እንደሆነም ይታወቃል፡፡ ለዚህም አእምሮ ንጉሴ የተባሉ ሰው ቅራት በተባለው መጽሀፋቸው ወሎ ገዳማት ውስጥ የሚገኙ የብራና መጽሀፍትን በመጥቀስ ሙሴ ወሎ ውስጥ አሁንም መደጊም ተብላ የምትታወቅ ቦታ እንደኖረ፤ ካህኑ ራጉኤል (ዮቶርም) የዛ አካባቢ ሰው እንደሆነ ይጠቁማል፡፡ ይህችም መደጊም የምትባል ቦታ የነገደ ምድያም መታሰቢያ ናት፤ ምድያም የሚለው ስምና መኖሪያ ከዚሁ ጋር ትይይዝ አለው ብለዋል፡፡ ይህና መሰል ምንጮች ቤተ አማራ ቀድሞውንም ከእስራኤላዊያን ጋር (ከነሱ በፊትም ሊሆን ይችላል፡፡ ጠለቅ ያለ ነገር አለው እዚህ ላይ ሌላ ጊዜ ልናገረው የምችለው) ግንኙነት እንዳለው ነው፡፡
እናም ምንም ቢሆን አንኮራበትም፤ አማራ ታይታ አይወድም፤ በልቡ ትሁት ነው እንጅ፤ እንናገር ካልን ሌላም ብዙ አለ፡፡ በጌምድር ወይም መላው ቤተ አማራ የአማራ ብቻ ደም ሳይሀን የእስራኤልም ደም በውስጡ አለበት፡፡ አማራ ሲደመር እስራኤል ማለት ነው፡፡ የዚህ ሀሳብ መነሳትም ፋይዳው የቤተ አማራን የኩሽና ሴማዊ ድብልቅነት ለማስረዳት ነው፡፡ ባለፈው ይህ ህዝብ መለኮታዊ ቀረቤታ አለው ስልም ይህንን ሁሉ ግንዛቤ ውስጥ በማስገባት ነው፡፡ የአምላክ ህዝብ ነው ብየ መጻፌም በዚህ እና ለወደፊት በምናገረው ምክንያት ነው፡፡ የወለፈንዴዎቹ ምድር ግን እስራኤላዊያ እንዳልነበሩብ፤ ይልቅም ንጉሱ ካሌብ በቤተ አማራ ላይ እንዲሰፍሩ እንዳደረጋቸው ከታች ያለው የእንግሊዝኛ ጽሁፍ ይጠቅሳል፡፡ በእርግጥ የአክሱም ነገስታት ራሳቸው አማሮች ነበሩ፡፡ ከዛም ቀደም ብሎ ከእስራኤላዊያን ጋር ግንኙነት ነበራቸው፡፡ ይህ ክፍል የአሁኑ ትግሬ ከአክሱም ስልጣኔ ጋር ግንኙነት ሊኖረው እንደማይችል በሌላ ጽሁፍ ስመለስ የምዳስሰው ይሆናል፡፡
ለናሙና ያህል አንድ ወለፈንዴዎች የሚያምኑትን የፈረንጅ አፍ ማስረጃ አስቀመጫለሁ፡፡ ከላይ ያልኩትን የሚያጠናክር ሀሳብ ነው የያዘው መጽሀፉ፡፡ ሌላም ብዙ ማስረጃ እንጠቅሳለን-እንዳስፈላጊነቱ፡፡ ለዛሬው ከ (Ben-Rafael and Yochanan (2005), “Is Israel One? Religion, Nationalism, and Multiculturalism Confounded.” Vol. 5. BRILL: Leiden.) መጽሀፍ የሚከተለውን አንቀጽ ጀባ ብለናል፡፡
These authors document that: “Latter, Jews who retreated from the coastal areas of Ethiopia established an independent state in the Lake Tana region. In the sixth century, Jews also settled in the Semyen region by order of King Kaleb. In the thirteenth and fourteenth centuries, Beta Israel lost its independence and many Jews were forced to convert Christianity” (p.150). They also mapped the location of the Bet Israel: “Most of Beta Israel lived in the north of Ethiopia, between the Takkaze River to the north, Lake Tana to the east, the Blue Nile to the south, and the border of Sudan to the west. They inhabited villages of their own, the most important and best known of which were near the town of Gondar” (p.152).
ማሳሰቢያ ለሙስሊም ቤተአማራ፡- ይህ ጽሁፍ ሀይማኖታዊ ይዘት የለውም፡፡ ለመልስ ብቻ የተዘጋጀ ነው፡፡ ከአሁኑ የቤተ አማራ አጀንዳ ጋር አንዳች ግንኙነት የለውም፡፡ ለወለፈንዴዎች ስንመልስ እንዲህ አይነተ ነገር ውስጥ ስንገባ ቅር አንዳትሰኙብን በቤተ አማራ ስም ይቅርታ እንጠይቃለን፡፡ ይቅርታ፡፡
መለክ ሐራ ከቤተ አማራ
እውን አማራና ትግሬ ተዋግቶ ያውቃልን?
=========================
በማህበራዊ ሚዲያም፤ በመሸታ ቤትም፤ በመንግስት መዋቅርም፤ በግለሰቦችም ንግግር ሁልጊዜ የትግራይ ሰዎች ደጋግመው የሚናገሩት ነገር አለ፡፡ እርሱም አማራን በጦርነት ማሸነፋቸው፤ አማራ ጀግና እንዳልሆነ፤ አማራ ፈሪ እንደሆነ፤ ትግሬ ግን ጀግና እንደሆነ፤ አማራ ፉከራ ብቻ የሚዎድ እንጅ የእውነት ጀግና እንዳልሆነ፤ ትግሬ ግን በተግባር ጀግና የሆነ እና አሸናፊ ጦረኛ፤ እንዲሁም በታሪክ ሁልጊዜ አማራን ሲያሸነፍ እንደኖረ መለፈፍ ነው፡፡ ደርግን ማሸነፋቸውን ትግሬ አማራን እንዳሸነፈ አድርገው ነው የሚያወሩት፡፡ ግን ሁልጊዜ ሳስበው ግርም ይለኛል፡፡ የሚያስገርመኝ እስካሁን ሲናገሩ የሰማኋቸውና የማውቃቸው ትግሬዎች አንድ ላይ ተስማምተው የሚያምኑት እምነት መሆኑ ነው፡፡ መገረሜን እተውና ስለድንቁርናቸው ደግሞ በጣም አፍርላቸዋለሁ፡፡ እውነት እውነት እላችኋለሁ እኔ ስለነሱ ድንቁርና ሁልጊዜ ሽምቅቅ ብየ እንዳፈርኩ ነው፡፡
ድንቁርናቸው የሚጀምረው አማራና ትግሬ በታሪክ አንድም ጊዜ ነገድ ለይቶ ጦርነት ውስጥ አለመግባቱን አለማወቃቸው ነው፡፡ በመሳፍንት መካከል የነበረው የስልጣን ሽሚያ ፈጽሞ የነገድ ጦርነት አለመሆኑን ለማወቅ መማር ብቻ ሳይሆን ሰው መሆን ብቻውን በቂ ነው፡፡ ደርግን አሸነፍን ሲሉ ያው ወደሌላው ነገር ሳልገባ አሸንፍን የሚሉትን ብቻ ልውሰድላቸውና ደርግ አማራ አልነበረም፡፡ ደርግ እንዴውም አማራን በተለያዩ ምክንያቶች በጭካኔ ይጨፈጭፍ የነበረ፤ በአማራ በጣም የተጠላ ነበር፡፡ ለዚህም ደርግን ፊት ለፊት በመግጠምም ሆነ ውስጡን ቦርቡረው በመጣል የአማራ ልጆች ቀዳሚውን ሚና ይወስዳሉ፡፡ ወታደሩም ከሁሉም የኢትዮጵያ ህዝብ የተውጣጣ እንጅ አማራ ብቻ አልነበረም፡፡ እነ አጅሬ ግን ደርግን አማራ ነው አማራውን አሸነፍን ብለው ራሳቸውን ያታልላሉ፡፡ እውነቱ ግን አይደለም አማራ እንደአማራ ገጥሟቸው ይቅርና ጉናን እንኩዋ የጋይንት ሰው አላሳልፍ ብሉአቸው በሽማግሌና በተማጽኖ በደርግም ጅልነት ነው ያለፉት፡፡ 25 ጊዜ ማጥቃት አድርገው ከጉና ተራራ ለመውረድ ሞክረው አልቻሉም፡፡ አንድ ወረዳ የማይሞላ አማራን ማለፍ አልቻሉም ነበር፡፡
ሻዕብያ ሊውጣቸው በነበረ ጊዜ እንኳ አማራ ነው ሄዶ ተረባርቦ ያተራፈቸው፡፡ ዘመድ መስለውት፡፡ በኋላ ጀርባውን እንደሚወጉት ሳያውቅ፡፡ ባድመ፡ ጾረና፡ ዛላምበሳ ምናም ተብሎ የዘመቱት የሰፈሬ ልች እንኳ ስንቶቹ እንደቅጠል ረገፉበት፡፡ ሰፈራችን አንድ ሰሞን የለቅሶ ድንኳን ብቻ ሆኖ በሁሉም ቤት ሀዘን ነበር፡፡ ያንን አድርጎ፤ ህይወቱን ገብሮ እነሱን ያተረፈ ህዝብ ግን ዛሬ ፈሪ ሲባል መስማት ከህመም በላይ ነው፡፡ ይባስ ብሎ መሳለቂያ ሲሆን ማየት ይዘገንናል፡፡ ያኔ ትግራይ ውስጥ ውትድርና የሚሄድ ጠፍቶ አልፎ አልፎ በግዴታ ነበር እየታነቀ የሚወሰደው፡፡ አማሮች ግን አገር ተደፈረ ሲባሉ እውነት መስሏቸው የምዝገባ ጣብያውን ሁሉ አጨናንቀውት ነበር፡፡ በፈቃደንነት ሄደው ነበር እንደ ተርብ ያለቁት፡፡ ዛሬ ያ ሁሉ ተረስቶ የወያኔ ካድሬዎች ግፍንና ጡርን ተናግሮ በማያባራው አፋቸው ሲሰድቡት እና ሲገፉት ይውላሉ፡፡
በታሪክ ትግሬ አማራን አሸነፈ የሚሉት ተረትም ከመመጻደቅ እንደማያልፍ ብናውቅም በእነሱ ማፈራችን አልቀረም፡፡ እውነት ለመናገር ከአክሱም ውድቀት በኋላ ትግሬ የሀይል የበላይነት ወስዶ የመንግስትን ስልጣን መያዝ የቻለው እንኳ ሁለት ጊዜ ብቻ ነው፡፡ አጼ ዮሐንስ 4ኛ እና አሁን ወያኔ፡፡ ከአክሱም ውድቀት በፊት የነበረው መንግሰትም የትግሬ ስለመሆኑ መተማመኛ የለም፡፡ ዛሬ እዛ አካባቢ ላይ ትግሬ መኖሩ ጥንት ገዥ መደቡ ወይም ነገስታቱ ትግሬ ነበሩ ማለት ሊሆን አይችልም፡፡ ከአክሱም ውድቀት በፊት የነበረው መንግስት የትግሬ ነበር ብለን ብንወስድ እንኳ ከዛ በሁዋላ ባለው 1300 አመታት ገደማ ውስጥ ትግሬ የመንገስት ስልጣን ያያዘው እንደተጠቀሰው ሁለት ጊዜ ብቻ ነው፡፡ የአገውና የአማራን የግዛት ዘመን አንድ ላይ እንደምረዋለን፡፡ እርሱም የቤተ አማራ የስልጣን ዘመን ስለሆነ አንድ ላይ ነው የሚቆጠረው፡፡ ከዚህ 1300 የቤተ አማራ ዘመን ላይ 17 አመት የአጼ ዮሐንስ 4ኛ እና 23 አመት የወያኔን አመት ደምረን እንቀንሳለን፡፡ 1300-40 = 1260 አመት ልዩነት ያመጣል፡፡ ስለዚህ 40/1260 = 0.03 ንጽጽር ያመጣል፡፡ ይህ ቁጥር ከትልቁ 1260 አመት አንጻር ምንም ዋጋ የሌለው አቅራቢያ-ዜሮ ነው፡፡ ስለዚህ የወያኔ ካድሬዎች ኩራት ከንቱ ቅዠት ነው፡፡ የማይወዳደር ነገር ይዘው ነው የሚንጦለጠሉት፡፡ (ቁጥሩን ግን በገደምዳሜው ከ 7ኛው ክፍለ ዘመን ብየ ነው የወሰድኩት፡፡ ትክክለናውን አክሱም የወደቀችበትን ወርና አመት ምህረት የሚያወቅ ሊተባበረኝ ይችላል)፡፡
ምንም እንኳ አማራና ትግሬ በታሪኩ ተዋግቶ ባያውቅም አሁን ግን ሆነ ብለው እየቆሰቆሱት እንደሆነ እያስተዋልን ነው፡፡ ጥንቃቄ ቢያደርጉ ይበጃቸዋል፡፡ ይህንንም ንግግራችንን እንደ አጉል ፉከራ ነው የሚቆጥሩት፡፡ አማራ በማንም ላይ ፎክሮ አያውቅም፡፡ በአስተሳሰቡም ግለሰቦችን እንጅ የሚጣላው ቡድኖችን ተጣልቶ አያውቅም፡፡ የዳበረ ባህላዊ የፍትህ ስርአት የታደለ በመሆኑ በደል የፈጸሙበትን ነጥሎ ለፍርድ ያስቀምጣል እንጅ እንደሌላው ሁሉ ቡድናዊ ጠላት አለኝ ብሎ አስቦ አያውቅም፡፡ አሁንም የወያነ ካድሬዎች በጸባያባችን የሌለውን ቡድንን ጠላት ብሎ የማሰብ በሽታ እኛ ላይ ልትጭኑብን አትሞክሩ፡፡ እዛው ራሳችሁ ተሸክማችሁት ዙሩ፡፡ ሁሉን እንወዳለን፡፡ ይህ ግልጽ ነው፡፡ ለይተን የምንጠላው ቡድን የለም፡፡ ለይተን የምንጠላውና ለፍርድ የምናስቀምጠው ግለሰብ ግን ይኖራል፡፡ ይህም ግልጽ ነው፡፡
መለክ ሐራ ከቤተ አማራ
የቤተ አማራ ጥቅም ሳይከበር የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ሊከበር አይችልም!
አንድ የኮካዎች መድረክ ላይ ነው ፤ አብዛኛው ተሳታፊዎች ተጋሩ ናቸው። ክርክሩ ደግሞ በዋነኝነት ስለ ትግራዩ አረና ፓርቲ ሲሆን በተወሰነ መልኩም ቢሆን ህዋሃትን በተመለከተ። አረና ፓርቲ ማለት እንደ እነ አብርሃ ደስታ አይነት እንቁ ወጣት ፖለቲከኞችን እና አንጋፋውን አቶ አሰገዶም ገብረ ስላሴን ያቀፈ ሲሆን ህዋሃት ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ በትግራይ ክልል የተቋቋመ የፖለቲካ ድርጅት ነው። ፓርቲው አዲስ እንደመሆኑ መጠን የራሱ የሆነ ተቋማዊ ድክመቶች እንደሚኖሩበት መገመት ቢቻልም ባለው አስቸጋሪ ሁኔታ እንደ አንድ ፋና ወጊ የፖለቲካ ፓርቲ ግን ለሚያደርገው ትግል ሊበረታታ የሚገባው ተቋም ነው። በተለይም ደግሞ ኢትዮጵያዊ አቋሙ ለድርድር የሚቀርብ አይደለም።
ከክርክሩ እንደተረዳሁት ከሆነ ይህ ኢትዮጵያዊ አቋሙ በተለይም ደግሞ ከሌሎች የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሃይሎች ጋር የሚያደርገው ግንኙነት በህዋሃት ኮካዎች ዘንድ አልተወደደለትም።
አንደኛው ተከራካሪ(በነገራችን ላይ ይህ ኮካ እዚሁ ፌስቡክ መንደር የሚልከሰከስ እጅግ ዘረኛ የሆነ እና 'መለስ ኢየሱስ ነው' ብሎ የሚከራከር አይነት ቅልጥ ያለ ካድሬ ነው፤ስራውን እውቅና ላለመስጠት ስሙን ለጊዜው ትቸዋለሁ) 'አረና ማለት እኮ የደላላዎች ፓርቲ ነው' ሲል ወቀሳውን ያቀርባል። የደላላዎች ፓርቲ ማለቱ ለባለፉት 24 አመታት ተነጥሎ የሚገኘውን የትግራይን ህዝብ ከሌላው ኢትዮጵያ ወንድሙ እና እህቱ ጋ ሊያገናኝ ጥረት ማድረጉን እንደ ክህደት ቆጥሮት እንደሆነ ለመረዳት ነብይ መሆን አያሻም።
በተቃራኒ የቆመ አንድ እውነተኛ ተከራካሪ ግን እንዲህ ሲል መልስ ሰጠው " የአረና ሃጢአት ሃገር ውስጥ ከሚገኙ ፓርቲዎች ውስጥ ትብብር መፈለጉ ነው ? ያንተ ፓርቲ (ህዋሃትን ማለቱ ነው) አይደለም እንዴ የሃገሪቱን ብሄራዊ ጥቅም ለጎረቤት ሃገር አሳልፎ ከመስጠት አልፎ በሃገር ውስጥ ሁሌ ሁከት የሚፈጥረው" ሲል እጅግ የሚያረካ መልስ ሰጠው። አንዳንዴ እንደዚህ አይነት ደፋር እና ግልጽ ጥቂት የትግራይ ወጣቶችን ሳይ ለምን እንደሆነ አላውቅም ውስጤን ደስ የሚል ስሜት ይሰማዋል ። ነገር ግን ይህ የአበደ የህዋሃት ካድሬ እጅ መስጠት አልፈለገምና የሚከተለውን እጅግ የሚያቆስል መልስ ሰጠ።
"ብሄራዊ ጥቅም ምናምን ተወው እና ቢያንስ ፓርቲያችን በትግራይ ጉዳይ ላይ ድርድር አያውቅም። አረና ፓርቲ ግን የትግራይን ጥቅም ለነፍጠኛ ሃይሎች (የፈረደበት አማራ መሆኑ ነው) አሳልፎ ሲሰጥ ብዙ ጊዜ አይቻለሁ" አለ። መቼም የሚያናድድ አባባል ነው። እውን አብርሃ ደስታ ወይንም አቶ አሰገደ ገብረስላሴ ስለ ኢትዮጵያዊነት አጥብቀው ከመጮሃቸው ውጭ መቼ እና የት ይሆን የትግራይን ህዝብ የሚጎዳ ነገር አድርገው ለአማራው ወይንም ለሌላው ህዝብ አሳልፈው የሰጡት? ለካ በሃገሪቱ ስላሉ ብሄሮች ፍትህ፤ ነጻነት እና እኩልነት ማውራት የትግራይን ህዝብ ጥቅም አሳልፎ መስጠት ነው እንደነዚህ ሰዎች አባባል።
እንደዚህ ኮካ እና እንደ ብዙዎች የህዋሃት አመራሮች እና ካድሬዎች አስተሳሰብ ከሆነ የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም ከተከበረ የትግራይ ጥቅም ይጎዳል፤ መጀመሪያ የትግራይ ጥቅም ሲከበር ብቻ ነው ብሄራዊ ጥቅም ብሎ ነገር ከዚያ በኋላ ሊወራ የሚችለው ማለት ነው። የኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም መቃብር ቢወርድም ህዋሃት የትግራይን ህዝብ ጥቅም እስካስከበረ ድረስ ሺህ አመት እንዲገዛ ነው የእነዚህ ሰዎች ምኞት። በተረፈ በሃገሪቱ ሰላም፤ የብሄር እኩልነት እና ነጻነት ተከበረ ማለት የትግራይ ጥቅም ገደል ገባ ማለት ነው።
እናስ ቤተ አማህራዎች ሆይ እንዴት ብለን ነው ከእነዚህ ሰዎች ጋ ልንኖር የምንችለው? እንዴት ነው በእናንተ መቃብር ላይ የእኛ ጥቅም ይከበር ከሚሉን ሰዎች ጋ አብረን የምንዘልቀው? እንዴት ነው የትግራይ ህዝብን ጥቅም ከኢትዮጵያ ብሄራዊ ጥቅም መከበር በላይ ከሚያዩ ሰዎች ጋ ለአንዲት ደቂቃ እንኳ አብረን መዋል የምንችለው? እረ በእውነት ያማል። ማንስ ነው የአማራ ህዝብ ጥቅም ሳይከበር ብሄራዊ ጥቅም ሊኖር አይችልም ብሎ በድፈረት የሚከራከረው ወገን? እኒህን ጥያቄዎችን ቆም ብለን ራሳችንን ስንጠይቅ የቤተ አማራ ምስረታ አስፈላጊነት ፍንትው ብሎ ይታየናል።
እኛ በአንድነት ስም ራሳችንን ስናታልል ሰዎች መቃብራችንን እየቆፈሩ ነው። የጥፋት ውሃ ሁሌም እየተደገሰልን ነው፤ ከተማሰው ጉድጉድ ማምለጥ የምንችለው ደግሞ እኛነታችንን በቅጡ ለይተን በጋራ አይሆንም ማለት ስንችል ነው። የአማራ ህዝብን ጠቢብነት፤ ጀግንነት እና ጽናት ተላብሰን ወደ አንድ መድረክ መምጣት ከቻልን ከቶ ሊያቆመን የሚችል ሃይል አይኖርም። የቤተ አማራ ምስረታ የምርጫ ጉዳይ ሳይሆን ግዴታ የሆነበት ወቅት ላይ እንገኛለን። የአንድነት ሃይሎችም ስራችሁን ስሩ። እናንተ ቀድማችሁ ኢትዮጵያን ነጻ አውጥታቹህ እኛንም ነጻ ካወጣችሁን እሰየው፤ እስከዚያው ግን ስለ አንድነት እያወራን ቆመን የምንጠብቅበት ሰአት የለንም። ሁሉም ራሱን ነጻ ያውጣና ከዚያ በኋላ ስለ አንድነት እና አብሮ መኖር እናዎራለን። ትዳር በመፈቃቀድ እንጅ አንዱ የበላይ አንዱ የበታች ሆኖ በብረት ሰንሰለት የሚኖርበት ተቋም አይደለም እና ዛሬውኑ እንነሳ ፤ጉዟችንን ወደ ተሰፋይቱ ምድር ወደ ቤተ አማራ እናድርግ።
መልካም የሆሳእና በአል ለሁሉም ቤተ አማራዎች!
አክባሪያችሁ ካለሁበት ቤተ-አምሓራ
በመጨረሻም ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ መልስ ጻፉልኝ!
________________________________
እኛ ግን ታድለን! ቤተ አማራ እድለኛ ነው፡፡ ልጅ ከአባቱ ጋር የሚያደርገው ንግግር ብቻውን ብዙ ነገር ይመሰክራል፡፡ እኔ ብላቴና መለክ ሐራ ከታላቁ አባታችን ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ ፊት እቆም ዘንድ ምንድን ነኝ፡፡ እንዲሁ እድለኛ ሰው፤ አባት ያለኝ ሰው ነኝ፡፡ መላው ቤተ አማራ ኩሩ፡ ደስም ይበላችሁ፡፡ እኛ መካሪ አባት የሌለን ትውልድ አይደለንም፡፡ በጣም የሚገርመው እኔ ነኝ ያንጓጠጥኳቸው፡፡ እርሳቸውስ ልብን በምታቀልጥ ትህትና ተናገሩኝ፡፡ ጽሁፋቸውን ሲዘጉ ““ቤተ አማራ” ያልከው ይሻላል ብለህ ነው?” በሚል የይቻላል አይነት ጥያቄ ነው፡፡ እናም ቤተ አማራ ትክክለኛ መጠሪያችን መሆኑን ታላላቆቻችንም ያምኑበታል ማለት ነው፡፡ በቃ ቤተ አማራ ጽኑእ ስማችን ነው፡፡ ግን ፕሮፌሰርን አንድ ቦታ በጣም ያበሳጨኋቸው ይመስለኛል፡፡ ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡ ለትልቅ ሰው የሚበጅ አማርኛ አልመረጥኩ ይሆናልና በውነቱ በደለኛ ነኝ፡፡ እንዴው ዛሬም ሳልናገር የማላልፈው ግን እርሳቸው ከታች እንደሚታየው ስለአማራ ደፍሮ በመጻፍ እኔ የመጀመሪያ አይደለሁም፤ መለስና ፕሮፍ. መስፍን ተነጋግረውበታል አይነት ነገር ብለዋል፡፡ እኔ ግን እነዚህ ሁለት ሰዎች የተነጋገሩት ለምስክርነት ይበቃል ብየ አላምንም፡፡ ሙሉ ንግግራቸው አማራ አለ የለም በሚል ንትርክ ነው የሚያልቀው፡፡ ልክ አማራ የማይዳሰስ ረቂቅ ነገር የሆነ ይመስል አለ የለም ሲባባሉ ማየት እንዴት ያሳቅቃል፡፡ እና እነዚህ ሁለት ሰዎች ስለ አማራ ደፍረው ጻፉ ወይ ተናገሩ ሳይሆን የሚባለው አማራን ደፈሩት ነው፡፡ ከሰውነት ወደ አለ የለምነት ክርክር አወረዱት ማለት ነው፡፡
እንግዲህ አባታችንን እጅግ እያመሰገንኩ የእርሳቸውን ሙሉ ጽሁፍ አንዲትም ሆሄ ሳትቀየር፤ ሳትጨመርና ሳትጎድል አስቀምጫለሁ፡፡ በድጋሜ አመሰግናለሁ፡፡
እርሳቸው ይቀጥላሉ፤
ለአቶ መለክ ሐራ፤
ወጣትነትህን ከመልእክትህ በመረዳት “አንተ” እያልኩ ልመልስ። ስለ ጻፍክልኝ አመሰግናለሁ። “ድንግርግር ያልከውን ብዙ አላብራራህልኝም” እል እነደሆነ ነው እንጂ፥ ወጣት ሆነህ መልስ ሰጠኸን የሚል ግምትስ በአእምሮየ አልመጣም። ለማንም ሰው በምንም ጉዳይ ላይ መጻፍ ድፍረት ሊሆን አይችልም።
1. “በመጀመሪያው ጽሁፍዎ ትልቅ ቁም ነገር የሚሆነው የአማራን ጉዳይ ደፍረው ርእስ ሰጥተው መጻፍዎ ብቻ ነው” ስለ አማራ መናገር ድፍረት አይመስለኝም፤ የመጀመሪያውም አይደለሁም። ብዙ ተጽፏል።
2. “አማራ በአሁኑ ሰአት የእርቅም ሆነ የእርግማን ሀሳብ ይዞ ቢመጣ ማንም የሚሰማው የለም፡፡” ካልተሞከረ፥ ሰሚ ሳይኖር ይቀራል፤ ከተሞከረ ሰሚ ሊኖር ይችላል። ካለመሞከሩ መሞከሩ ይሻላል። “የሚሰማው የለም” ብሎ ሙከራውን መከላከል ተገቢ አይመስለኝም።
3. “በምን መንገድ አማራን ከጥፋት መታደግና በኢትዮጵያ ውስጥ ሊኖረው የሚችለውን ሚና በቦታው ማሰቀመጥ እንደሚችል በውል አላሳዩም፡፡ ደግሞስ ተራድኦ ድርጅት መመስረት እንዴት ቅድሚያ ጉዳይ ሊሆን እንደቻለ ምንም የሰጡት ማብራሪያ የለም፡፡” የምፈልገው መጠኑ እንዲሰፋ ነው እንጂ እርዳታውስ ተጀምሯል፤ የሆነ ያልሆነ ምክንያት እያመጣ የሚያደናቅፍ ሰይጣን እንዳይገጥመው እንጠንቀቅ። ደግሞስ፥ ከምን ጉዳይ ነው ለዕርቅ ድርጅት ቅድሚያ የሰጠሁት? መቅደም ያለበትን ጉዳይ እንዴት ነው ወደኋላ የጎተትኩት? አማራው እያለቀ ነው። ከምን መከራ ላይ እንዳለ አንተም ገልጸኸዋል።
4. “እንደኔ እንደኔ ግን ሌሎች መደረግ ያለባቸውን አማራጮች አንድ በአንድ አስበውባቸው ይሄው የተራድኦ ድርጅት ጉዳይ የበለጠ አሳማኝና በቀላሉ ተግባራዊ ሊሆን የሚችል ነው ብለው አምነውበት ነው የሚል እምነት የለኝም፡፡” “የምትጽፈው ያላመንክበትን ነው” ማለትህ ነው። ይኸ ቅር ያሰኘኛል። መልስ እንዳልሰጥህም ገፋፍቶኝ ነበር።
5. “አማራ በዘር የለም ካሉ በዘር ነገድ የሆነ ሌላ ማነጻጸሪያ ሃሳብ ማቅረብ ነበረብዎ፡፡” ይኽንን ነጥብ ወድጀዋለሁ። አቶ መለስና ፕሮፌሰር መስፍን በአማራው ጉዳይ ላይ ሲወያዩ (“በዚህ ርእስ ስተች የመጀመሪያው ደፋር አይደለሁም” ያልኩትን አስታውስ) አቶ መለስ፥ “አማራ የሚባል ዘር የለም ካልክ፣ ዘር ላይ የተመሠረተ ጎሳ ወይም ነገድ የለም” ብሎ ነበር። እኔም የምለው እኮ፥ ስለአማራው ብቻ ተናገርኩ እንጂ፥ ይኸንኑ ነው። በዘር የተመሠረተ ጎሳ/ነገድ የለም። የሌለን ከሌለ ጋር ማነጻጸር አይቻልም። ስለአማራው የጻፍኩት፥ የምተቸው ስለ አማራ ስለሆነና “አማራ የሚባል ሕዝብ አለ” የሚሉ ሰዎች ዘርን መሠረት አድርገው ስለሚተቹ ነው።
6. “አማርኛ ተናጋሪዎች” ይኽ ስም የወጣውም “አማራ የሚባል ዘር የለም” የሚለውን አስተሳሰብ ለመግለጽ ነው። ጥሩ ስም አይደለም፤ ግን የተሻለ ስም አልተገኘም። “አፍ መፍቻው አማርኛ የሆነ” የሚልም መግለጫ ተሰንዝሯል። እስቲ አማራጭ አምጣ። “ቤተ አማራ” ያልከው ይሻላል ብለህ ነው?
ከሰላምታ ጋር፤
ጌታቸው ኃይሌ
አማራን በመንፈሳዊ እይታ ሳየው የእግዚአብሔር ህዝብ እንደሆነ ይሰማኛል
___________________________________________
ታሪኬን ዳሰስኩ፡፡ የንቡረ እድ ኤርምስን ንግግር ሰማሁ (ከመልከ ጼዴቅ ካህን እስከ አእዛን ያለው ቢላል ድረስ አማሮች ናቸው ይላሉ)፡፡ አማራን አሰብኩት፡፡ ከመንፈሳዊ ህይወቱ አንጻር ቃኘሁት፡፡ አማራ ጥንት ከኦሪት በፊት የታወቀው የግዮን ምድር ነዋሪ ነው፡፡ ግዮንም ገነትን የሚያጠጣው ወንዝ ነው፡፡ እና ቤተ አማራን አንዳች የቅድስና ነገር፤ ምስጢራዊ ነገር እንዳለው መረመርሁ፡፡ ብዙዎች ነገሮች እውነትም የአምላክ ህዝብ እንደሆነ እንዳምን አደረጉኝ፡፡
እኔ የማውቀው አማራ ባህርያትም የሚከተሉት ናቸው፡፡ ተመችቶትም ተቸግሮም ጸሎት፡ ጾምና ምጽዋት አይረሳም፡፡ ማታ ማታ ለልጆቹ ስለወዲያኛው አለም ከማስተማር አይቦዝንም፡፡ ወደ መለኮታዊ ቦታ ለመሄድም አይሰንፍም፡፡ ምድሪቷንም ገዳማትና የምናኔና ስውር ቤተ ጸሎት አድርጓታል፡፡ ራሱ ጨፈቃ ውስጥ እየኖረ የአምላኩን ቤት አስጊጦ ይሰራል፡፡ ልጆቹን እያስራበ እንኳ የእግዜር እንግዳ ብሎ ያስተናግዳል፡፡ ቤት ለእንግዳ ብሎ አልጋውን ለቆ መሬት ላይ ወይም በረንዳ ላይ ይተኛል፡፡ ሲጸልይ አገሩን አማን ቀየውን ሰላም አድርግልን፤ ወንዞችን እስከገደፋቸው ምላልን ይላል፡፡ የጽድቅን መንገድ አጥብቆ ይሻል፡፡ እየተበደለ እንኳ በቀልን ለአምላኩ ይተዋል፡፡ ይውጋህ ሲሉት ይማርህ ይላል፡፡ ሲረግሙት ይመርቃል፡፡ ልግስናን ለልጆቹ ያስተምራል፤ ራሱም ይኖረዋል፡፡
አቡነ ተክለ ኃይማኖት የተባሉ ቅዱስ ሰው አለው፡፡ በምድር ላይ የሚመለክ ኃይለ ሥላሴ የተባለ ሰው አለው፡፡ ከ150 አመታት በፊት የዛሬውን ሁኔታ በትንቢት ሳይዛነፍ ያስቀመጡት ሸህ ሁሴን ጅብሪል የተባሉ ሰው አለው፡፡ አንዳንድ በሽታዎችን ፈጽሞ የሚያድኑ ጥበባት አሉት፡፡ ብቻ አማራ ለአምላክ ቅርብ እንደሆነ የሚያሳዩ ብዙ ነገሮች አሉት፡፡ ከሁሉም በላይ ደግሞ በአለም ላይ በከፊል እንኳ በማንም ቅኝ ገዥ ያልወደቀ ጥቁር ህዝብ ነው፡፡ ጥቁር ላይ አድሎ በሚደረግባቸው ቦታዎች ሁሉ አማራ ራሱንና ሌላውን ጥቁር ያስከብራል፡፡ ለምሳሌ የአሜሪካ ቤተ መንገስት ለመጀመሪያ ጊዜ የገባ ጥቁር መሪ አማራ ነው፡፡ ከድንቅ የአለም ሰዎች ንግግሮች የተመዘገበ የአማራ ነው፡፡ ክብሩን በሀይሉ ያስከበረ አማራ ነው፡፡
እና ይህ ህዝብ ፈተና ይበዛበታል፡፡ የአምላክ ህዝብ ደግሞ ፈተና ይበዛበታል፤ የሚፈታተነው ነገር አያሌ ነው፡፡ ለዛሬ መንፈሳዊ ጽሁፍ ጻፍኩ…ራሱ የአማራ መንፈስ በል በል አለኝ፡፡ እምነት የሌላችሁ ቤተ አማሮች እንዳትቀየሙኝ አስቀድሜ ይቅርታ እጠይቃችኋለሁ፡፡ይቅርታ፡፡ የራሴ ግላዊ አቋም ነው፤ የቤተ አማራ አይደለም፡፡
የትንታጎቹ አገር ወልቃይት ብረሳሽ ቀኜ ትርሳኝ!
ድል ለቤተ አማራ
መለክ ሐራ ከቤተ አማራ

የወልቃይት ሳምንት
============
በመጀመሪያ እባብ ወንዝ ሞላበት፡፡ በዚያም ሰው ነበረ፡፡ ሰውም ወንዙን ይሻገር ነበር፡፡ እባብም ሰውን አለው “እባክህ አሻግረኝ”፡፡ ሰውም ልቡ ራራ፡፡ እባቡንመ ራሱ ላይ ጠምጥሞ አሻገረው፡፡ ወንዙን በተሻገሩ ጊዜ ግን እባብ ከሰው አልወርድም አለ፡፡ ሰውም አለው “ውረድ እንጅ፤ ውላችን እንድትወርድ አልነበረምን?” እባብም አለው “እኔ አልወርድም” ፡፡ እባቡም ወንዝ ያሻገረውን ባለውለታውን ሰው ነድፎ ገደለው፡፡
ይህ ብሂል በቀጥታ ቤተ አማራ ላይ የደረሰ ነው፡፡ በጎንደር ሰሜንና ሰሜን ምእራብ ወልቃይትጠገዴ የሚባል ዘመን መቆጠር ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የቤተ አማራ እጣ ክፍል የሆነ ምድር አለ፡፡ ይህ ምድር ሀብታም፤ ባለጸጋና ለም ነው፡፡ ሰውም ደግና ጀግና ነው፡፡ የእምነትና የእውነት አገር ነው፡፡ ወደር የለሽ ጀግንነት የባህርይው የሆነ ህዝብም ይኖርበት ነበር፡፡ ይህም ወልቃይት ተርቦም ተጠምቶም አያውቅም፡፡ በድሮው ጊዜም የምርቱን ውፍረትና ጠንካራ አምራችነቱን ለማሳየት በጥይት ይመታ ነበር፡፡ የጥይት እርሳስ ምርቱን የበሳችበት ወልቃይት እንደሰነፍ ይቆጠራል፡፡ እርሳስ ግን ምርት ውስጥ ተወሽቃ በቀረች ጊዜ ወልቃይቴው አራሽ አንደፋራሽ ጀግና ይባላል፡፡ ወልቃይት ለእንግዳ አልጋውን ለቆ መሬት ላይ የሚተኛ ህዝብ ነው፡፡ ሲቆጣ አሞራን በጥይት ከሰማይ የሚያወርድ ነው፡፡ ወልቃይት ለእመብርሀን ዝክረኛ እንጀራ ቆርሶ አይሰጥም፡፡ ነውር ነው፡፡ ለዝክረኛ ሙሉ እንጀራ ይሰጣል እንጅ፡፡ ወልቃትም ለእንግዳ ያለው እምነት ለፈጣሪው ካለው እምነት ቢተካከል እንጅ አያንስም፡፡ ይህም ወልቃይት ከጥንት የታወቀ ጀግና፤ ምድሩም እስከ ኤርትራ ምድር የሚዘልቅ፤ በምእራብም ሱዳን ብቻ የሚያዋስነው ነበር፡፡
ከዘመናትም በአንዱ ወያኔ የሚባል ወንበዴ ከትግራይ ወገን ተነሳ፡፡ ይህም ወንበዴ ትግራይን ከደርግ አገዛዝ በጉልበት ነጥቆ ነጻ ካወጣ በኋላ መላዋን ኢትዮጵያ መውረር ፈለገ፡፡ ለወረራም መሰናዶውን ካጠናቀቀ በኋላ ወደ መሀል ኢትዮጵያ ለመዝለቅ በወልቃይት ማለፍ የግድ ሆነበት፡፡ የእባብ ጸባዩንም በመቀየር በመለሳለስ ከወልቃይት ልብ ውስጥ ገባ፡፡ ሰው አማኙም ወልቃይት ለዚህ እባብ እልፍኝና አዳራሹን ወለል አድርጎ ከፍቶ አስገባው፡፡ በእባቡም ምላስ የተንኮል ንግግር ተታለለ፡፡
ይህ ወያኔ ለአመታት ወልቃይት ውስጥ በቆየባቸው ጊዜያት ሁሉ ቅን መስሎ ኖረ እንጅ እውነተኛ ጸባዩን አልገለጠም ነበር፡፡ ወልቃይትም ለዚህ ወያኔ ወተት እያጠጣ አኖረው፡፡ ከአዝርእት ፍሬውም አልለየውም፡፡ የሰባውንም እያረደ ቀለበው፡፡ ሴት ልጆቹም ውሀ እንዲቀዱለትና ማገዶ እንዲለቅሙለት አደረገ፡፡ ቁስለኛውንም እቤቱ እያስታመመ ያድን ነበር፡፡ የሞተውንም ጉድጓድ ቆፍሮ አልቅሶ ይቀብር ነበር፡፡ ከማሳውም እሸት እየቀጠፈ እንካ ብካ ይለው ነበር፡፡ የከርሞ ሰው ይበልህ ብሎም ይባርከው ነበር፡፡ እነሆ ወልቃይት ካለው ነገር ሁሉ ሰስቶ አንዳችም ነገር አላስቀረበትም፡፡ ያለውን ሁሉ ሰጠው እንጅ፡፡ በክፉ ቀን መሸሸጊያ ሆነው፡፡ በዚህም ግብሩ ደርግ ለተባለው ገዥ ሰለባ ሆነ፡፡ እንደምንድር ነው ነገሩ ቢሉ ወንበዴ ትደብቃለህ፤መንገድ ትመራለህ፤ ስንቅም ትሰጣለህ እየተባለ፡፡ ይህ ወያኔ ግን በውጭ መልካም እየመሰለ በውስጥ ክፉ ነገር ያስብበት ነበር፡፡ ማታ ማታም ቢላ ይስልለት ነበር፡፡ ይህም ወያኔ ክፉውን ቀን ሁሉ በወልቃይት ጉያ ተሸሽጎ አሳለፈ፡፡ ጎለመሰም፡፡ መላዋን ኢትዮጵያንም ተቆጣጠረ፡፡ ነገር ግን ሳይውል ሳያድር ወልቃይትን ማረድ ጀመረ፡፡ ወንድ የሆኑትን ሁሉ ገደለ፡፡ ሴት ልጆችና ሚስቶችን ለራሱ አደረገ፡፡ ጫካ እንደሚመነጠር ሁሉ ይህ ወያኔም ወልቃይትን ሁሉ መነጠረ፡፡ ወልቃይትም ባጎረስኩ እጀን ተነከስኩ አለ፡፡ ነገሩ ሁሉ እጸድቅ ብየ ባዝላት ተንጠልጥላ ቀረች እንደተባለው ሆነ፡፡ ወልቃይትም ወርቅ ባበደርኩ ጠጠር፤ እህል ባበደርኩ አፈር ተመለሰልኝ አለ፡፡ ብዙውም የወልቃት ክፍል ፈጽሞ ጠፋ፡፡ በባእዳንም ተወረረ፡፡ የተረፈው ወልቃይትም ቁጥሩ እንደዋልያ ተመናምኖ ባልሞት ባይ ተጋዳይነት ውጭ ነብስ ግቢ ነብስ ሆኖ አለ፡፡ ወያኔም እለት እለት ይገድለዋል፤ በየለቱም ያስረዋል፤ በየለቱም ይሰድበዋል፤ በየለቱም ያሳድደዋል፡፡ በውኑ ወልቃይት እንደ ቃየን ተቅበዝባዥ ሆነ፡፡ መከራውም ማለቂያ አጣ፡፡ የሚረዳውም አልተገኘም፡፡ የለደረሰበትም በደል አልተሰማለትም፡፡ ዛሬ የዚህ ወገናችን በእሳት ላይ ተጥዶ እየተጠበሰ መሆን በእውኑ ለቤተ አማራ ትልቅ ሞት ነው፡፡
መላው ቤተ አማራም እንግዲህ ይህንን ሳምንት ወልቃይትን በማሰብ፤ ስለወልቃይት በመጻፍ፤ ፎቶ በመለጠፍ፤ አይዞሀ አይዞሽ በመባባል እንዲያሳልፈው ስንል ቤተ አማሮች ይህ እዲሆን በጎ ነው ብለናል፡፡
ከዚህም በታች አገራቸውን ተቀምተው በስደት አውስትራልያ በሚገኙበት እስራኤል በስደት ዘመኑ ሁሉ ያደርግ እንደነበረው ሁሉ ወልቃይትን እያሰቡ የሚያሳይ ዘፈን ነው፡፡ እነዚህ የምታዩአቸው ቤተ አማሮች አገር የላቸውም፡፡ ከሞት መንጋጋ ያመለጡ ናቸው፡፡ ይሀች የሚዘፍኑባት አዳራሽ ብቻ ናት አገራቸው፡፡ ያንን ብሩክና ማርና ወተት የሚፈስሰውን ምድራቸውን ግን ተቀምተዋል፡፡ እነርሱም ባተዋርና መጻተኛ ናቸው እንጅ አገር የላቸውም፡፡
ድል ለቤተ አማራ!
መለክ ሐራ ከቤተ አማራ
ከትግራይና ከኦሮሚያ የሆኑ ሰወች ስለቤተ አማራ የመገንጠል ሀሳብ ሙድ ሊይዙ ሲሞክሩ እኔ በቃ ከልቤ ነው የሚያስቁኝ ፡፡ smile emoticon ማለት ዊይይይ እናንተም??? በሚል አይነት
ዋና ጠንሳሾች፤ ለህዝብ መገንጠል የሚለውን ሀሳብና ቃል በሀገር ደረጃ እንዴት እንደሚከወን ያሳዩ ሰወች??? ጠዋት ማታ አንቀጽ 39 ምንትስ ምንትስ እስከመገንጠል እያሉ ሲሰብኩ የኖሩ ??? !!! pacman emoticon የሆነ ስለመገንጠል ሙድ መያዝና መቀለድ በእናንተ አያምርም ፤ እንጨት እንጨት ይላል ቀልዱ፡፡ ምክንያቱም አሁንም ቢሆን በሁለት አማራጮች እንደምትንቀሳቀሱ ጸሀይ የሞቀው ነገር ስለሆነ፡፡ ይልቅ ቤተ አማራወች በናንተ የ40 አመት የ”ልገነጠል ነው ፣ተገንጠሉ “ ቀደዳ ሙድ ይዘው እንዳይሆን መጠርጠር ነው፡፡ smile emoticonWho knows ? ወይም ተስፋው ለመነመነው የአማራ ወገን ሁለተኛውን መንገድ እያሳዩ ነው፡፡
ወይ መቆየት ደጉ ፤ እነሱም ስለ አንድነት መልካምነት በቀጥታም ይሁን በስላቅ ለአማራ ሊሰብኩ ??? ሃሃሃ
"ምጥ ለእናቷ አስተማረች" ማለት ይሄኔ ነው፡፡ wink emoticon grin emoticon
ፕሮፌሰር ጌታቸው ሀይሌን የምታገኙ ይሄንን ንገሩልኝ
አማርኛ ተናጋሪና የእርቅና የተራድኦ ድርጅት ብሎ ድንግርግር
===============================
መቸም እኔ አንድ ብላቴና ነኝና ለእርስዎ አማራን በሚያክል ትልቅ ህዝብና በገጠመው አንገብጋቢ ጉዳይ ሳቢያ የተሰማኝን መጻፌ ከማንጓጠጥ ቢቆጠርብኝ እሽ ብየ እንደምቀበል ማመን እወዳለሁ፡፡ ሁለት ጊዜ በጻፉት ላይ የተሰማኝን ልናገር፡፡ በመጀመሪያው ጽሁፍዎ ትልቅ ቁም ነገር የሚሆነው የአማራን ጉዳይ ደፍረው ርእስ ሰጥተው መጻፍዎ ብቻ ነው፡፡ የተቀረው ሀሳብ አካዳሚያዊና ከወቅቱ መሰረታዊ ችግር በብዙ መልኩ የራቀ ነው፡፡ ጉዳዩ አሳስቦዎት መጻፍዎ የሚደነቅ ይሁን እንጅ የጽሁፉ መነሻና ግብ-ጥቆማ አማራን በአሁኑ ወቅት ከገጠመው ችግር የራቀ ነው፡፡ የእርስዎ ዋናው ሀሳብ አማራ የእርቅና የተራድኦ ድርጅት ያቋቁም ነው፡፡ ምናልባት አማራ አሁን ያለበትን ሁኔታ ያልተገነዘቡት መሰለኝ፡፡ እውነታው እንዲህ ነው፡፡ አማራ በአሁኑ ሰአት የእርቅም ሆነ የእርግማን ሀሳብ ይዞ ቢመጣ ማንም የሚሰማው የለም፡፡ ለምን ቢባል ሰይጣን ውዳሴ ማርያም ስለደገመ ቤተ መቅደስ ገብቶ ይቀድሳል ማለት አይቻልም፡፡ በሁለተኛው ጽሁፍዎ እንደጠቀሱትና እኔም እንደምለው ላለፉት 40 አመታት በአንድም በሌላ መንገድ የኢትዮጵያ ዘውጌ ብሔረተኞች ዋና ስራቸው አማራን ዲያብሎስ አድርጎ ማሳየትን ነው፡፡ ስለዚህ አንድ መናኝ ከአምላክ በዲያብሎስ በኩል የተላከለትን ህብሰት ይብላው ወይስ ይወርውረው የሚል መስቀለኛ ጠርዝ ላይ ያስቀምጣል፡፡ የእርቅና የተራድኦ ድርጅት ሲሉ አማራው ይህንን ድርጅትና አላማ የሚያደርሰው ለአማራው ነው ወይስ አማራን በዲያብሎስነት ለሚመለከተው ለሌላው ብሄረሰብ ነው? የሚሰማ ሳይኖር ስለምንም ነገር መናገር አይቻልም፡፡ እኔ እንኳን በእድሜየ በደረስኩበት አማራ የተባለ ሰው ያመጣው ሀሳብ የነፍጠኛና መሰል ተቀጽላ ስሞች እየተሰጠው ሲንቋሸሽ እና ሲብጠለጠል ነው የማውቀው፡፡ ከልምድ እንደተረዳሁት አማራ ያመነጨው ማናቸውም ሀሳብ በሀሳብነቱ ሳይሆን በአማራነቱ ነው የሚመዘነው፡፡ ይህ በድርጅቶች ብቻ የሚደረግ እንዳይመስሎዎት፡፡ በእያንዳንዱ ግለሰብ ላይ የሚንጸባረቅ በተዋረድ አገር አቀፋዊ ችግር የሆነ እንጅ፡፡ ስለዚህ ሰሚው የማይሰማው ተናጋሪ ባይናገር ይሻለዋል፡፡
ሁለተኛው የጽሁፉ ጭብጥ ተራድኦ ድርጅት ያሉት ነገር ነው፡፡ ተራድኦ ድርጅት ሲሉ አማራን እንደምን ቢስሉት እንደሆነ ሊገባኝ አልቻለም፡፡ ድርጅቱ ማንን ምን ብሎ፤ ለማን ምን አድርጎ፤ በምን መንገድ አማራን ከጥፋት መታደግና በኢትዮጵያ ውስጥ ሊኖረው የሚችለውን ሚና በቦታው ማሰቀመጥ እንደሚችል በውል አላሳዩም፡፡ ደግሞስ ተራድኦ ድርጅት መመስረት እንዴት ቅድሚያ ጉዳይ ሊሆን እንደቻለ ምንም የሰጡት ማብራሪያ የለም፡፡ እንደኔ እንደኔ ግን ሌሎች መደረግ ያለባቸውን አማራጮች አንድ በአንድ አስበውባቸው ይሄው የተራድኦ ድርጅት ጉዳይ የበለጠ አሳማኝና በቀላሉ ተግባራዊ ሊሆን የሚችል ነው ብለው አምነውበት ነው የሚል እምነት የለኝም፡፡ እንደሚገባኝ የተራድኦ ድርጅት የሚያቋቋም ግለሰብም ሆነ ቡድን እንቅስቃሴው ሊደረግበት በታሰበው ቦታና ሁኔታ ውስጥ በሚኖረው ጫናና ሚና ይወሰናል፡፡ አማራ በአሁኑ ሰአት በተራድኦ ድርጅት ነገሮችን መለወጥ የሚስቸውለው ቦታና ሁኔታ ላይ ስላለመገኘቱ በደንብ ያሰቡበት አልመሰለኝም፡፡ የተራድኦ ድርጅት አቋቋሞ የእርቅ ስራ የሚሰራ ግለሰብም ሆነ ቡድን ላቅ ያለ ወይም እኩላዊ ሚና ሊኖረው ይገባል፡፡ ከዚህ በተጻራሪ አማራው ለእርቅ የሚሄድባቸው ብሄረሰቦች በማናቸውም ረገድ ከአማራው የተሻለ ቦታና ሚና ያላቸው ናቸው፡፡ ይህም የእርስዎን ሀሳብ ተቀባይነቱን ፈተና ውስጥ ይጥለዋል፡፡ ከዚህም አንጻር ስናየው አማራው ማቋቋመ ካለበት የተማጥኖ ድርጅት ወይም በሀይል ራስን የማስከበር ድርጅት ብቻ ነው፡፡ የተራድኦ ድርጅት አቋቁሞ ስለእርቅ ለመናገር ተሰሚት፤ አቅም፤ ህግ ያለበት አገርና መንግስት እና መጠነኛ የመደማመጥ ወይም የመደመጥ እድል ሊኖር ግድ ነው፡፡ በእነዚህና ሌሎች ጉድለቶች የተነሳ ያነሱት ሀሳብ የማያስኬድ ይሆናል፡፡
በሁለተኛው ጽሁፍዎም የእርቅና የተራድኦ ድርጂትን ጉዳይ ደግሞው አንስተዋል፡፡ ከላይ የተገለጸው ሀተታ ይህንንም የሚመለከት በመሆኑ መድገም አላሻኝም፡፡ ከዚህ ይልቅ በሁለተኛውም ጽሁፍዎ መግቢያ ላይ አንድ አማራን እና አማራነትን ሊጎዳ የሚችል አገላጽ ተጠቅመዋል፡፡ በአመዛኙ ጽሁፉን ብውደወም ቅሬታ ተሰምቶኛል፡፡ እርሱም አማራ በዘር የለም በባህል ግን አለ ያሉት ነገር ነው፡፡ አማራ በዘር የለም ካሉ በዘር ነገድ የሆነ ሌላ ማነጻጸሪያ ሃሳብ ማቅረብ ነበረብዎ፡፡ አማራ በዘር የለም ሲሉ ሌሎች ግን በዘር ነገድ ናቸው የሚል አንድምታ ያዘለ ንግግር ነው፡፡ እናም በባህል አማራ አለ ብለው በዘር የተካደውን ወይም የተገደለውን አማራ ነፍስ ለመዝራት ሞከሩ፡፡ የማህበረሰብ ሳይንስ ጥናቶች እንደሚያሳዩት ነገዶች ወይም ጎሳዎች ባህላዊ እንጀ ደማዊ ወይም ፍጥረታዊ አይደሉም፡፡ ሁሉም የባህል ውጤቶች ናቸው፡፡ በዘር እንደዚህ የሚባል ነገድ የለም፡፡ በተለይም ወደ ኢትዮጵያ ስንመጣ በዘር የሚደረገው ክፍፍል በባህላዊው ተጽእኖ የተዋጠ ነው፡፡ እንደጽሁፍዎ አንድምታ እና እንደ ብዙዎች እምነት ማንም ነገድ የባህል ውጤት መሆኑ እያታወቀ አማራ ብቻ የዘር ሀረጉን ከአዳምና ሄዋን እንዲስብ መጠየቁ በጣም የሚያስገርም ጉዳይ ነው፡፡ ልብ ብለን ብናየውና ይህንን የእርስዎን የባህል ኑባሬ ብንመረምረው አማራ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉትና ከጠፉት ነባር ነገዶች አንዱ ነው፡፡ ወደኋላ ሄዶ አማራ መባል በዚህ እርግጠኛ ቦታና ጊዜ ተጀመረ ብሎ መናገር ያለመቻሉም አንዱ የአማራን ለረጅም ጊዜ የቆየ ነገዳዊ ህልውና የሚያረጋግጥ ነው፡፡ ከአማራ መፈጠር በኋላ እየተሰነጣጠቁ ወይም እየፈለቁ የነገድነት ካባ የደረቡ ብዙ ነገዶች የህልውና ጥያቄ ሳይነሳባቸው ቀደምቱ አማራ ላይ የሚደረገው ዘመቻ ግራ የሚያጋባ ነው፡፡ አንዳንድ ሰዎች አማራን ሀይማኖታዊ ስያሜ ለመስጠት ይዳዳሉ፡፡ ይሁንና ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በፊት ስለነበረው አማራ በውል የሚናገሩት ነገር የለም፡፡ አማራ ከ16ኛው ክፍለ ዘመን በፊት ከነበረ እንዴት ከኋላ በመጣው ሀይማኖት ማእቀፍ ስር ሊጠራ እንደቻለ የሚሉት ነገር የለም፡፡ አማራ ከ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኋላ ነው የተከሰተው ከተባለ ደግሞ እንዴት ክርስቲያን የሆነው አገው አማራ የሚል ሀይማኖታዊ ስያሜ እንዳልተጎናጸፈ የሚሉት ነገር የለም፡፡ አማራና እስላም የሚለው ሀይማኖታዊ ገለጣ አገውና እስላም ወይም ክርስቲያን አገውና እስላም ማለት ይሆንን ብለው አልጠየቁም፡፡ እንደዛስ ከሆነ ማን የሚባለው ነገድ ነው ከእስልምና መከሰት በኋላ አማራ የተባለው? ከዛስ በፊት ማን ባል ነበር ይህ ህዝብ?
በሁለተኛው ጽሁፍዎ ያነሱት ሌላው ጉዳይ አሁንም አማራን አማራ ብሎ ከመጥራት የተለመደ የመተናነቅ ነገር ይስተዋልበታል፡፡ አማርኛ ተናጋሪ ብሎ እንደመጥራት መቸም ትዝብት ላይ የሚጥል ነገር የለም፡፡ አማርኛ ተናጋሪ ሁሉ አማራ ከሆነ እንግዲህ 80 በመቶው የኢትዮጵያ ህዝብ አማርኛ ይናገራል፡፡ ስለዚህ ይህ ሁሉ አማራ መሆኑ ነው፡፡ እንደኔ እንደኔ ይህ አገላለጽ በጣም ችግር ያለበትና አደገኛ ነው፡፡ መቸም እንግለዝኛ ተናጋሪ ሁሉ እንግሊዝ ነው ወይም ዌልስ ነው የሚል ሰው ያለ አይመስለኝም፡፡ በምንም መስፈርት ተናጋሪው ከመነጋገሪያው የሚቀድም ህልውና ነው ያለው፡፡ ከእንግሊኛ በፊት እግሊዞች ነበሩ፡፡ አማራም ከአማርኛ በፊት ነበር፡፡ አማራ የሚባል ህዘዝብ መኖሩ ነው አማርኛ የተባለውን ቋንቋ እንዲፈጠር ያደረገው፡፡ አማራ አማርኛን ፈጠረ እንጅ አማርኛ አማራን አልፈጠረውም፡፡ ለምን ቢባል አማርኛ የነገዱን ስም ይዞ የተፈጠረ ተቀጽላ ነው፡፡ የተወሰነ የአማራ ማንነት ያለው ተናጋሪ ያልነበረው ቋንቋ በምንም መልኩ የነገዱን መጠሪያ ተከትሎ ሊሰየም አይችልም፡፡ ለዚህ ማሳያ ብንወስድ ግእዝ በራሱ ትርጉም ያለው ቋንቋ ነው፡፡ የማናቸውም ነገድ ተቀጽላ መጠሪያ አይደለም፡፡ ምናልባት ወደኋላ ሄደን አግአዝያን የሚባለው ህዝብ መጠሪያ ነው ብለን ካላሰብን በቀር፡፡ እናም አማርኛ ተናገሪ ሁሉ አማራ አይደለም፡፡ አማራን በራሱ ቋንቋ ተናጋሪዎች መሰየም አድሎአዊ ነው፡፡ የአባትን ስምና ድርሻ ቀመቶ ለልጅ ወይም ለሩቅ ዘመድ እንደማደል ይቆጠራል፡፡ በዚህ አካሄድ እኮ አማራ ማለት ራሱ አማራው ሳይሆን በተለያዩ ከተሞች የሚኖሩ አማርኛ የሚናገሩ አማራ ያልሆኑ ነገዶች ማለት ነው፡፡ ይህ ልክ ያልሆነ አረዳድም ነው አማራውን የሚናገርለት የሌለው ያደረገው፡፡ አማርኛ የሚናገር ሁሉ ልክ የአማራን ጉዳይ እንደተናገረ ወይም ወክሎ እንደተናገረ በመቆጠሩ አማራው አፉን ተቀማ፡፡ በራሱ ችግሩን አቤት ብሎ ማስረዳት የማይችል ሆነ፡፡ በከተማ አማርኛ ተናጋሪ ሰዎች አማራው አፉን ተነጠቀ፡፡
መለክ ሐራ ነኝ ከቤተ አማራ
"ይድረስ በሕወሃት መለዮ ለባሾች ውስጥ የቤተ ኣምሓራ ልጆች
ሕዝባችሁ በደርግ ዘመነ መንግስት ያለ ምንም ቅድመ ሁናቴ በየቦታው ሲገደል መኖሩን ታውቃላችሁ። በሻለቃ መላኩ ተፈራ ኣስፈጻሚነት የጎንደርን ወጣቶች ፳፬ ሰዓታት በግፍ እንድረሸኑ የተደረገበት ትዕዛዝ ከዘመኑ ኣበይት የዘር ማጥፋት እርምጃዎች ኣንዱ ነበር። ኣሁን ደግሞ ህወሃት ስልጣን ከመያዙም በፊትም ጀምሮ ደርግን ሳይሆን ኣምሓራን ለማትፋት ነው ኣላማችን ብሎ ከተነሳበት ጊዜ ጀምሮ ሌት ተቀን እኛን ለማጥፋት እየሰራ ይገኛል። በኣደባባይ ከገደሉትና ካሳረዱት ሕዝባችን በተጨማሪ ድብቁን የዘር ማጥፋት ዘመቻ እያከናወኑ ይገኛሉ። ለኣብነት ያህል ወደ ፫ ሚሊዮን ኣምሓራ ጠፍቷል ያሉት ኣቶ መለስ በተወሰነ መልኩ የህወሃትን የውስጥ ፖሊሲ መሳካት ያማለከት የኣምሓራ ህዝብ ውድቀት ነበር። በየቦታው ያለ ምንም ወንጀል ደመ ክልብ ሁኖ የቀረው ህዝባችን እርሳቸው ከገለጹት በላይ ቢሆንም መሰረታዊ ጉዳዩ ግን ኣሁንም እራሳችንን ማዳን እንዳለብን ለመስራት እንደምንገደድ ማወቁ ነው።
ከዚህም ባለፈ ተቀናሽ ሰራዊት ወደ ህዝብ ሲመለስ ቫይረስ በ ክትባት መልክ እንደሚሰጠው ይታወቃል። በዚህም የተነሳ የኣምሓራን ህዝብ የዘር ማጥፋት ፖሊሲ ለማሳልጥ ህወሃት የሚጠቀመው ኣንዱ መንገድ ነው። ስለሆነም ቤተ ኣምሓራን ለማቆም በምናደርገው ሁለንተናዊ ዘመቻ ከጎናችን በመሆን ትውልዳችን ይቀጥል ዘንድ፤በህወሃት ኣመራርነት የተሳለብንን ቢላዋ ሁሉ መመከት እንድንችል ኣብሮነታችሁ ያስፈልገናል። ይህን መረጃ በማካፈል የምታውቁትን ቤተ ዘመድ ወይም ጓደኛ የትግላችን ኣካል ማድረግ ሕዝባዊ ግዴታ መሆኑን ለማሳሰብ እንወዳለን።"
ዣንጥራር ከቤተ ኣምሓራ
የቤተ-አማራን የኢኮኖሚ ምሰሶዎች ከአሁኑ እናስባቸው (ራስ የማነ ከቤተ-አማራ)
ቤተ አማራ - የአማራን ሕዝብ ከጭቆና አስተዳደር ማላቀቅ ብቻ ሳይሆን ከዚያም በሁዋላ ሕዝቡን በተለይ በኢኮኖሚው ዘርፍ ተጠቃሚ ማድረግ ዋና አላማው ነው። ስለዚህ በኢኮኖሚ የበለፀገ ሕብረተሰብ መፍጠር ዋና አላማችን ነው። በኢኮኖሚ የበለፀገ ሕብረተሰብ ለአምባገነኖች ለመገዛት ፍቃደኝነት በፍፁም አይኖረውም የሚል ጠንካራ እምነት አለን። በአለም ዙሪያ ያሉ ያደጉ አገሮች በሙሉ ዲሞክራቲክ መሆናቸውን ስናይ ይህ በአጋጣሚ የሆነ ነገር እንዳልሆነ አንገነዘባለን። እነዚህን አገሮች ጉልበተኛ መጥቶ ልግዛችሁ ቢላቸው እንደማይገዙ ማስተዋልም አያዳግተንም። አይ እነሱ አገሮች እኮ ዲሞክራሲ ከሆኑ በኋላ ነው ያደጉት የሚል ሰው ካለ - እውነት ነው ዲሞክራሲ እድገት ያመጣል - ሐሳቡን በነፃነት ወደ ተግባር መለወጥ የሚችል ሕዝብ መበልፀጉ ጥርጥር የለውም። እንደገናም ደግሞ የበለፀገ ሕዝብ ከዲሞክራሲ በቀር የሚመጥነው አስተዳደር እንደሌለም የታወቀ ነው።
እኛ ስለሚኖረን ኢኮኖሚ ስናስብ አሁን ካሉን ነገሮች ጀምረን በሂደት የሌሉንን ነገሮች ወደ መኖር እየቀየርናቸው እንሄዳለን። አልተጠቀምናቸውም እንጅ በጣም ብዙ ነገሮች አሉን። ችግሩ በዛሬው የፖለቲካ አሰላለፍ አማራን የሚጠቅም ነገር ከማሰብ በላይ ትልቅ ወንጀል የለም። ስለዚም መጠቀምም አንችልም።
ታዲያ ያሉንን ነገሮች በመዘርዘር እንጀምራ?
እስኪ ካደጋችሁበት አካባቢ አልተጠቀምንበትም እንጂ ይሄን እኮ እንዲህ ብንሰራበት ኖሮ ስንቱን ሰው ይመግብ ነበር የምትሉትን አስቡት። በcomment section ላይ በአንድ አንቀጽ ይጻፉት - የት አንደሚገኝ - ምን ሊሰራበት እንደሚችል ይንገሩን። ካሁኑ እቅድ ውስጥ ይገባል። አስቀድሞ የታቀደ ደግሞ አፈፃፀሙ የድርስ ድርስ ስለማይሆን ፍፃሜው ያምራል። ጠቀሜታውም ከፍ ያለ ይሆናል።
የሚከተሉትን የኢኮኖሚ ምሰሶዎች በሚቀጥሉት ተከታታይ ጽሁፎች ይዘን እንመጣለን።
1. ከምንም በላይ ዋናው ምሰሶአችን ሕዝባችን ነው። ትልቅ ደረጃ የደረሱ የተማሩ የተመራመሩ ሰዎች ቢኖሩንም አብዛኛው ሕዝባችን የገጠር ነዋሪ ነው። ሕዝቡ ለ21ኛው ክፍለ ዘመን የሚሆኑ መሰረታዊ ትምህርቶችንና ስልጠናዎችን እየወሰደ በከፍተኛ ፍጥነትና ሁኔታ ይከትማል (ወደ ከተማ ይገባል)። ከ70 - 80% በላይ የገጠር ሕዝብ ይዘን ማደግ የቀን ቅዠት ነው። ትንታኔውን በቅርብ ቀን።
2. ምስራቅ አፍሪካን መመገብ የሚችሉ ለም መሬቶቻችን። ከላይ በቁጥር አንድ እንደጠቀስነው ሕዝቡን እያስተማሩ ወደ ከተማ በማስገባት የእርሻ መሬቶቻችን አሁን ካሉን በላይ እንዲሰፉ ማድረግና የመጨረሻውን ቴክኖሎጂ በመጠቀም ምርታችንን በብዙ እጥፍ ማሳደግ። ትንታኔውን በቅርብ ቀን።
3. ጣና እና ሌሎች ሐይቆቻችን። ከእኛ ተርፎ የውጭ ምንዛሬ የሚያስገኝ የዓሳ ምርት። እንዴት? ትንታኔውን በቅርብ ቀን።
4. ተራሮቻችንና ለእርሻ የማይሆኑ መሬቶቻችን በደን ሙሉ በሙሉ ይሸፈናሉ። በአውሮፓ ሰማይ ላይ ሲበር በደኖች የቀና ቤተ-አማራ ካለ በእኛ ይደሰታል። ምን አይነት የዛፍ አይነቶችና መሬትን ከመሸፈን በተጨማሪ ምን አይነት ጥቅም ሊኖራቸው ይችላል? ትንታኔውን በቅርብ ቀን።
5. የቱሪስት መስህቦቻችን። የበለጠ እንዲታወቁና እንዲጎበኙ ምን ማድረግ አለብን? ትንታኔውን በቅርብ ቀን።
6. የኢንዱስትሪ መንደር ምስረታዎች ይጧጧፋሉ። በተለይም ለእርሻ የማይሆኑና የከርሰ ምድር ውሃ የሌላቸው አካባቢዎች ወደ ኢንዱስትሪነት ይቀየራሉ። ከገጠር ወደ ከተማ የሚገባው ሕዝብ ተጨማሪ የስራ እድሎች በኢንዱስትሪው ምክኒያት ይፈጠሩለታል። የግል ክፍሉ በሰፊው እንዲሳተፍ አስፈላጊው ማበረታቻ ይደረጋል። የቤተ-አማራ መንግስትም በተመረጡና አስፈላጊ በሆኑ ዘርፎች ኢንዱስትሪውን ያስፋፋል። ትንታኔውን በቅርብ ቀን።
7. የአገልግሎት ክፍሉ በአይነቱና በጥራቱ ይስፋፋል። የግል ክፍሉ በሰፊው እንዲሳተፍ አስፈላጊው ማበረታቻ ይደረጋል። ጉቦና የተንዛዛ አሰራር በውድ ቤተ-አማራዎት የባለቤትነት ስሜትና በመንግስታችን ጥረት ይወገዳል። የገዛ ቤቱን ቆሞ የሚያዘርፍ ሰው የለም። ቤተ-አማራም ቤቱን ከኢኮኖሚ ጠላቶች እዲጠብቅ የባለቤትነት መብትና ቁልፉን በእጁ ይረከባል።
ይህ ውድ የቤተ-አማራ ሕዝብን ወደ ትልቅ ኢኮኖሚ ኃይልነት ለመቀየር ለሚደረገው ያልተቆጠበ ጥረት እቅድ መያዣ ነው። ሃሳብ ይመነጫል። እቅድ ይወጣለትና ገና ሳይሰራ ፍፃሜው ይታያል። በእቅዱና በንድፈ-ሃሳቡ መሰረት ወደ አካልነት ይቀየራል። ቤተ አማራ እንዲዚህ ነው የሚሰራው። የረጅም ርቀት ጉዞ በአንድ እርምጃ ይጀምራል። ወደ ነፃነትና ወደ ብልፅግና ጉዞ እንኳን ደህና መጣችሁ።