Bete Amhara

Bete Amhara

Monday, June 15, 2015

"እንደ አማራ ብጽፍ ( ሄኖክ የሺጥላ )
በዓለም ታሪክ በሰው ልጆች እልቂት ( የግፍ ጥፋት ) የሚጠቀሱ ብዙ ሰዎች አሉ ። ከነዚህ ውስጥ የሚያውቀውም የማያውቀውም የሚያውቀው ምናልባት አውስትሪያዊው አዶልፍ ሂትለርን ነው ( አንዳንዶች ሂትለር ራሱ በዘሩ አይሁድ ነው ይላሉ ፣ ለምሳሌ ሊቭንግስተን ) ።
ታሪክ ብዙም ያላወራላቸው ፣ ግን ከአዶልፍ ሂትለር በላይ የዘር ማጥፋት ( የሰው ልጆችን የማጥፋት ተግባር የፈጸሙ ) ብዙ ናቸው ፣ ለምሳሌ ቤልጀማዊው ንጉስ ሊኦፖልድ ። ይህ ሰው ከ 10 እስከ 15 ሚሊዮን የሚጠጉ ኮንጎዊያንን በግፍ እንደገደለ ፣ እንዳስገደለ ታሪክ ይዘግባል ። እርግጥ የአውሮፓውያኖችን ገጽታ የሚያደብዝዝ ስለሆነ ይሄ ጉዳይ በየትምህርት ቤቱ የሚነገር ታሪክ አይደለም ። በይበልጥም በአሁኑ ሰዓት ለእንስሳ መብት የሚታገሉ አዛኝ ነጮች ባሉባት ምድር እንዲህ አይነት ጨካኝ ነጭ አያት ነበራችሁ ማለት ለነሱም የማይዋጥ ፣ ለተናጋሪውም የማያዋጣ ሀቅ ስለሆነ ፣ እንዃን ለሰው ለእንስሳ ሳይቀር አዛኝ መሆናቸውን እየተናገርን እንድንኖር ነውና የሚፈለገው ፣ ነጭ ክርስቶስ ፣ ነጭ መላእክ ፣ ነጭ ብርሃን ፣ ነጭ መልካም ነገሮችን እያመሳሰልን እንድናስብ እና እንድናሳስብ ነውና የሚፈለገው ስለ ልዮፖልድ ብናወራ ምን ዋጋ አለው ? ምን ዋጋ አለው ፣ አሁን መኪና እና ስልክ ፣ አውሮፕላን እና መርከብ ( ምናልባት ነጭ አይሆንም የመጀመሪያውን መርከብ የሰራው ፣ ግን የመጀመሪያውን ትልቅ መርከብ የሰራው ነጭ ነው ስሙም ኖህ ይባላል )፣ ብንናገር ፣ ለወባ መድሃኒት ያላገኝ ሰዎች ፣ ምን ብናወራ ያምርብናል ? ምንም !
የሆነው ሆኖ የጨካኞች ታሪክ ስላልተጻፈ የጭከና ተግባሩ አልተፈጸመም ማለት አይደለም ። አንዳንድ ጨካኞች እድለኞች ናቸውና ። አንዳንድ ጨካኞች ፣ ልክ እንደ ሊኦፖልድ በኛም ሀገር ፣ አሁን እኔ ባለሁበት ዘመን ከ ሁለት ሚሊዮን በላይ አማሮችን ገድሎ ( አሳዶ ፣ የማምከኛ መርፌ ወግቶ ፣ አፈናቅሎ ፣ በ ዔድስ በሽታ አስወርሮ ፣ እና ወዘተ ) አድርጎ ሲሞት ባለ ረአይ የተባለ መሪ አለ ፣ የዚህ ሁሉ በደል ፈጻሚ የሆነው ስርዓት ዛሬም ድረስ ስለ ህዝቦች እኩልነት እያወራ ፣ በስልጣን ዘመኑ ሁሉ አማራን በተለየ መልኩ እና በከፋ ሁናቴ በማጥፋት ሥራ ላይ ተሰማርቶ ያለ ስርዓት አለ ። እርግጥ ነው በወያኔ ስርዓት ያልተጎዳ ዘር የለም ፣ ግን ከራሳቸው መረጃ ላይ ብነነሳ እንዃ እንደ አማራ ያፈናቀሉት ፣ የነቀሉት ፣ የገደሉት ፣በበሽታ ፣ በድንቁርና ፣ በመሰረተ ልማት አልባነት የጎዱት ብሔር የለም ። አንዳንድ አስመሳይ ታጋዮች የትግራይ ሕዝብ የስርዓቱ ተጠቃሚ አልሆነም ይላሉ ፣ በእርግጥም የስርዓቱ ተጠቃሚ አልሆነም ይሆናል ፣ ትግሬ ግን የስርዓቱ ተጠቃሚ ነው ። አዎ የትግራይ ሕዝብ ስንል ፣ ሁሉም የሚል እንድምታ ከሆነ የሰጠነው ፣ እንግሊዝ ሀገርም ሁሉም እንግሊዛዊ የእንግሊዛዊነቱ ተጠቃሚ አይደለም ፣ ፈረንሳይም እንዲሁ ።
ቢያንስ ቢያንስ የትግራይ ሕዝብ የስርዓቱ ተጠቃሚ ባይሆንም እንዃ በስርዓቱ ተጠቂ አይደለም ። አይ የስርዓቱ ግፍ እና በደል ደርሶበታል የምትሉ ካላችሁ ፣ እስኪ እኔ አከሌ በዚህ ምክንያት ትግሬ በመሆናቸው ከደቡብ ኦሮሚያ ተባረሩ ፣ እነ አከሌ ትግሬ በመሆናቸው ባህር ዳር ላይ ሆቴል እንዳይገነቡ ተከለከሉ ፣ እና ወዘተ በሉን ። እስኪ ትግራይ ውስጥ አንድ ሆቴል ይሁን መደብር ያለው አማራ ካለ ንገሩኝ ? አረ ምን ትግራይ ላይ አሁን አሁን ባህር ዳር ላይ እንዃ ባለ ሆቴሉ እና ባለ ንግዱ የትግራይ ተወላጅ አይደለምን ? ስለዚህ አንድ ነገር ማለት ይቻላል ፣ የትግራይ ሕዝብ የስርዓቱ ተጠቃሚ ባይሆን እንዃ ስርዓቱን ግን ጠቃሚ ነው ፣ የትግራይ ሕዝብ የስርዓቱ ተጠቃሚ ባይሆን እንዃ በስርዓቱ ይሄ ነው የሚባል በደል እየደረሰበት ያለ ሕዝብ ነው ለማለት አልችልም ። እርግጥ በደል ደርሶበታል ከተባለ ፣ በደሉ የሚደርስበት እንደ አማራው አማራ በመሆኑ ( እሱም ትግሬ በመሆኑ ሳይሆን ፣ እነሱ ከማይፈቅዱት እና ከማይወዱት ስርዓት እና ማህበረሰብ ጋ በመወዳጀቱ ነው ። አብርሃ ደስታ የታሰረው ትግሬ በመሆኑ አይደለም ፣ አብረሃ ደስታ የታሰረው ትግሬ ሆኖ ስርዓቱን መበመቃወሙ ነው ። ትግሬነት የሥርዓት ደጋፊነት ባይሆን እንዃ ስርዓቱን ጠቃሚነት እንደሆነ የታመነበት ጉዳይ የሆነው ፣ ቆጥረን የማንጨርሳቸው ትግሬዎች የስርዓቱ ደጋፊነታቸውን በጭፍን ስለገለጹ ነው ።
ለምሳሌ የትግራይ ሕዝብ ስለ ጭካኔ ሲያወራ ፣ ትልቁ ምሳሌው ደርግ ነው ፣ ያም ቢሆን ደርግ ላይ አምጾ በርሃ ወርዷል ፣ ታዲያ እንደዚያ የሚያስፈራውን ደርግ ያልፈራው የትግራይ ሕዝብ እንዴት ወያኔን ፍርቶ ዝም አለ ? ምንም ማንቆለባበስ አያስፈልግም ፣ እውነቱ ወያኔ ምንም ክፉና ጨካኝ ቢሆንም ፣ ከራሳችን የወጣ ስርዓት ስለሆነ ከነ መርዙ እንዘለው ብለው በመወሰናቸው ነው ። ለዚህም ምልክቱ ፣ በሀገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን በውጭ ሀገርም ጭምር ( እኔ እስከማውቀው ድረስ ) በጣት የሚቆጠሩ የትግራይ ልጆች ብቻ ዛሬም ወያኔን ስቃወሙ ማየት ፣ በስርዓቱ ላይ ያላቸውን የልብ ፍቃድ የሚያሳይ መሆኑን ነው ። ይህንን ጽሑፍ እንደ አማራ ነው የጻፍኩት ። ሲመቸኝ እቀጥላለሁ !