Bete Amhara

Bete Amhara

Wednesday, July 15, 2015

ጎንደር፡--ወርቅ አበድሮ ጠጠር የተመለሰለት

ጎንደር፡--ወርቅ አበድሮ ጠጠር የተመለሰለት

ጎንደርና ትግራይ በጉርብትና ኖረዋል፡፡ ትግራይ በተፈጥሮ የተጎዳ ስለሆነ ጎንደር ከጥንት እስከ 1983 አ.ም ድረስ ከትግራይ የሚመጡ ሰዎችን ወገቧን ታጥቃ ስታስተናግድ ነው የኖረቸው፡፡ የጎንደር ህዝብ ለትግሬ አንድ ቀን በሩን ዘግቶበት አያውቅም፡፡ ለዘመናት ከትግሬ የሚመጡ ሰዎች የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ይሰጡ ነበር፡፡ ማነጽና ካብ መካብ የመሳሰሉ ሞያዎች ይሰሩ ነበር፡፡ በማሳ እየተቀጠሩ ይሰሩ ነበር፡፡ ስራ እንኳን ባይሰሩም በየድግሱ ተጠርተውም ሳይጠሩም ይስተናገዱ ነበር፡፡ ከእያዳንዱ የጎንደር ሰው ቤት አጠገብ ግባዛ ወይም ጎጆ ወይም በረንዳ ላይ ቆጥ መሳይ አልጋ ይሰራላቸውና እዛ ይኖራሉ፡፡ ስራ ሲኖር ይሰራሉ፡፡ ስራ ሳይኖር እንደቤተሰብ አብረው ይኖራሉ፡፡ ለሽያጭ የሚሆን ነገር ሲፈልጉም ቃርሚያ ይለቅማሉ፡፡ አማሮችም ቃርሚያ ተውላቸው ይላሉ፡፡ ከደግነታቸው ብዛት የጎንደር አማሮች አውድማ እንኳ ጨርሰው አይጠርጉም፡፡ ለትግሬዎች ተውላቸው እያሉ ትርፍራፊ እህል ይተውላቸዋል፡፡ ያንን ጠርገው ለራሳቸው ይወስዳሉ፡፡ በየመንደሩ እየሄዱ ደግሞ ሰባራ ማድጋ፤ ወንፊት፤ ምጣድ ወዘተ ይጠግናሉ፡፡ ለስራቸው ክፍያም ቤት ያፈራውን ይመገባሉ፤ ገንዘብ ይሰጣቸዋል፤ እንደገናም እህል ይሰፈርላቸዋል፡፡ ዘወትር የጎንደር ህዝብ ትግሬዎችን በቤቱ አስጠግቶ ያኖራል፤ ስራ ያሰራል፤ ከማህበራዊ ህይዎቱ ደሀ ናቸው፡ መጤ ናቸው ሳይል ያስተናግዳቸዋል፡፡ አንድም ጎንደሬ ለትግሬ ክፉ አይን አሳይቶ አያውቅም፡፡ የትግራይ መጻተኞች የጎንደር እንግዳ ሆነው ነው የኖሩት፡፡ ስንቶቹ ክፉ ቀን ያለፈላቸው በጎንደር ደግነት ነው፡፡

ወያኔ ወደ ስልጣን ሲመጣ ደርግ የጎንደርን ወጣቶች ስለጨፈጨፈ ከጎንደር ጋር ጠላትነትን አፍርቶ ነበር፡፡ የደርግ ወታደሮች ክብሩን ወዳድ የሆነውን የጎንደርን ህዝብ በብዙ መልኩ ተፈታትነውት ነበር፡፡ ባለትዳሮችን ሁሉ ይደፍሩ ነበር፡፡ ደርግን አምርረው በመጥላትም የጎንደር አማሮች ለወያኔ ስንቅ እያቀበሉ፡ የደከመውን እያሳረፉ፡ እየተንከባከቡ፡ መረጃ እየሰጡ፡ እያገዙ፡ አሳልፈው ወደ ጎጃም እና ሸዋ ላኩት፡፡ ከተወሰኑ ቦታዎች በቀር የጎንደር ሰው በሰላም ነበር አሳልፎ የሸኛቸው፡፡ ምግብ እያበላ፤ ዉሃ አያጠጣ፤ ደርግን ራሱ እየተዋጋ አመጣቸው፡፡

ግን አገር እንደተቆጣጠሩ ያደረጉት የመጀመሪያ ስራ ጎንደር ውስጥ የነበረን ንብረት ሁሉ ወደ ትግራይ ማጋዝ ነበር፡፡ የአርበኞች ገጀራ አልቀራቸውም፡፡ ፋሲለደስ ግቢ ውስጥ ገብተው ሰፈሩበት፡፡ ውስጡ ኖሩበት፡፡ ልብስ ሁሉ አስጥተውበት ይዉሉ ነበር ለረጅም ጊዜ፡፡ በመቀጠል ተሰሚነት ያላቸውን ሰዎች እያደኑ እየሰረቁ ጨረሷቸው፡፡ ከፊሎችን በመጠጥ ቤት ግርግር እያስመሰሉ ገደሏቸው፡፡ እስካሁን የት እንደደረሱ ያልታወቁ ብዙ ናቸው፡፡ የመብራት ማመንጫ አልቀረም ሲያግዙት፡፡ እንደአጀማመራቸው ጎንደርን ራስዋን የሆነ ትልቅ የጭነት ማሽን ቢገኙ የሚወስዷት ነበር የሚመስለው፡፡ በእርግጥ በተለያየ ጊዜ ቦታውን መውሰዳቸው አልቀረም፡፡

እያበላ እያጠጣ መንገድ እየመራ ያመጣቸው የወልቃይትና ጠገዴ አማራ የመጀመሪያው ገፈት ቀማሽ ሆነ፡፡ መሬቱን የትግራይን ምልስ ጦር በነዋሪነት አሰፈሩበት፡፡ ወንዶችን እያደኑ ገደሉ፡፡ ሴቶችን እያስገደዱ ልጅ ወለዱባቸው፡፡ በግፍ እየጨፈጨፉ ጨረሷቸው፡፡ ሁሉንም ያበላቸውን ያጠጣቸውን፤ ክፉ ቀን ያሳለፋቸውን የጎንደር ህዝብ አጎሳቆሉት፤ ገደሉት፤ በእድገት የአለም ጭራ እንዲሆን አደረጉት፤ መሬቱን ወሰዱበት፡ ወደትግራይ ለመውሰድ ያልተመቻቸውን ቦታ ሁሉ ለሱዳን ሰጡበት፡፡ ሰሊጥ አምራቹን ህዝብ የዋጋ ተመን እየጣሉ ምርቱን ራሳቸው ይረከቡታል፤ የአገራችን የአማራ ህዝብም ሲያለማ ከርሞ እርሱ እርቃኑን ይቀራል---እስከ ዛሬ ድረስ፡፡ ምንም አይነት የመሰረተ ልማት እንዳይደረግለት አደረጉት፡፡ ብዙ የጎንደር ህዝብ እስካሁን ድረስ በበቅሎ፤ ግመል እና በእግር ነው ረጃጅም ርቀት የሚጓዘው፡፡ ጎንደር ላይ የተመረተ ምርት ቀድሞ ሱዳን ገበያ ላይ ነው የሚውለው፡፡ የአማራ የሀብት ምንጭ መሬትና ከብት በመሆኑ ከብቶችን በመኪና እየጫኑ ወደሱዳን ለአመታት ሲያጓጉዙ ከረሙ--አሁንም ቀጥለውበታል፡፡ የዚህ ዋና አላማው ለራሳቸው ገቢ ማግኘት እና በሂደት አማራውን ከብት አልባ አድርጎ ስደተኛ ማድረግ ነው፡፡ ይህም ለወያኔዎች ጎንደርን እና ወሎን በግዛታቸው ስር የመጠቅለል አላማ ትልቅ አስተዋጽኦ ያደርጋል፡፡ አማራ ከብት ከሌለው መሬቱን ማረስ አይችልም፡፡ መሬቱን ካላረሰ ደግሞ ጥሎት ይሰደዳል፡፡ ያን ጊዜም ወያኔ ይረከበዋል፡፡

የወያኔ ታላቋ ሪፐብሊክ ህልም ትግራይ ብቻ ናት ብላችሁ የምታስቡ ተሳስታችኋል፡፡ የወያኔ የህልም ድንበር አባይ ወንዝ ነው፡፡ እርሱም ጎጃምን እና አብዛኛውን ወሎን ይጨምራል፡፡ ታላቋን ትግራይ ሲመሰርቱም ህዝቡን በማጥፋት ነው፡፡ ህዝቡ ካልጠፋ ከተቀረው የአማራ ወገኑ ጋር ሊነጠልና እሽ ብሎ ስለማይሄድላቸው ብቸኛው አማራጭ ህዝቡን ማጥፋት ነው፡፡ በሀያ አመት ውስጥ የጎንደርን ሲሶ መሬት ሲወስዱ ማንም ምንም አላላቸውም፡፡ በዚህ ሲሶ ምድር ውስጥ የሚኖርም ህዝብ በአብዛኛው ጠፍቷል፡፡ በዚህ ስሌት ከሄድን ከአስራ አምስት አመት በኋላ ሙሉ ጎንደር በእጃቸው ትሆናለች፡፡ ካሁኑ እንኳ ጃኖራን፤ ራስ ደጀንን እና ደባርቅና አምባጊዮርጊስን ለማካለል እየተንቀሳቀሱ ነው፡፡ በመማሪያ መጽሀፍቶቻቸውም የትግራይ ግዛት እንደሆኑ ለአዲሱ ትውልድ እያስተማሩ ነው፡፡ እነሱ ልጆቻውን ሲያሳድጉ ይሄ ይሄ ምድር ያንተ አገር ነው፤ ትግራይ ነው፤ እንጅ ኢትዮጵያ ነው እያሉ አይደለም፡፡ እናም በስሌቱ መሰረት ከ50 አመት በኋላ ጎጃምና ወሎ የተባሉ አገሮች አይኖሩም፡፡ እዛ የሚኖር አማራ የተባለ ህዝብም አይኖርም፡፡ ለዚህም ነው እቅዳችን 60 ወይም 70 አመት ነው የሚሉት፡፡ ይህ ጊዜ አማራን ለማጥፋትና የአማራን አገር ትግራይ ለማድረግ በቂ እንደሆነ አስልተውት ነው፡፡ በአሁኑ ጊዜ ደግሞ ህዝብን ማጥፋት ቀላል ሆነላቸው፡፡ በቴክኖሎጅ በመታገዝ ማንም ሳይሰማ ህዝብን መጨረስ ያስችላቸዋል፡፡ እያደረጉትም ነው፡፡ በአንድ ጊዜ አይደለም የሚጨርሱን፡፡ በዚህ ሰፊ የጊዜ እቅድ በዘዴ ነው፡፡ ቀስ በቀስ አማራ ተረት ሊሆን ነው፡፡

ለዚህም ማረጋገጫው የነጻ አውጭ ስማቸውን አለመቀየራቸው እና የጥላቻ ዘመቻቸው እየባሰበት መምጣቱ ነው፡፡ ለምን የትግራይ ህዝብ ነጻ አውጭ የሚለው ስማቸው አልተቀየረም ለሚለው መልሱ የትግራይ አስተማማኝ ነጻነት የሚታወጀው አማራ ሲያልቅ ወይም ተጽእኖ ማምጣት ወደማይችልበት አናሳ ጎሳነት ሲቀየር ብቻ ነው፡፡ አማራ እስከሚያልቅ ድረስ የትግራይ ነጻ አውጭነት ስምና ስራቸው ይቀጥላል፡፡ እነሱ ሞኞች አይደሉም፡፡ ለጊዜው የያዙት ስልጣን እና ያገኙት ድል አስተማማኝ እና ዘለቄታዊ እንዳልሆነ ያውቃሉ፡፡ ለዚህም ትግራይን ነጻ ማውጣት ገና ሂደት እንጅ ግብ ላይ አልደረሰም ይላሉ፡፡ የትግራይ ነጻነት ግቡን የሚመታው አማራ ጠፍቶ የአማራ ለም መሬቶች የትግራይ ሲሆኑ እና ተው ብሎ የሚገዳደራቸው አማራ ሲጠፋ ብቻ ነው፡፡ ይህም ማለት በእነሱ ስሌት ትግራይ የወታደራዊ ነጻነት እንጅ ያገኘቸው ገና የኢኮኖሚ ነጻነት አላገኘችም፤ በወደፊት ታላቅ ሪፐብሊክነት ደህንነትዋም ከአማራ ተጽእኖ ነጻ በምትወጣበት ቅርጽ አይደለም ያለችው፡፡ ስለዚህም የትግራይ ህዝብ ገና ነጻ አልወጣም ብለው እስከቀደመ ስምና ግብራቸው እንደቀጠሉ ናቸው፡፡ ያለ ምንም ጥርጥር ትግራይ ነጻ ሆነች የሚባለው አማራ ጨርሶ ሲጠፋ ብቻ ወይም ተመናምኖ አናሳ ሲሆን ብቻ ነው፡፡ እስከዛ ድረስ አማራን ማጥፋት እና የትግራይን የመሬት፤ የሀብትና መሰል ስፋትና ግንባታ መስራት ተጠናክሮ ይቀጥላል፡፡ የያዙት ድል ጊዜያዊ መሆኑን ይገነዘባሉ፡፡ ስለዚህም ይህንን ጊዜያዊ ድል መሰረት ለማስያዝ ተግተው ይሰራሉ፡፡ የኛ አማራም የክፋታቸው ልክና ጥልቀት ስላልገባው ያጅባቸዋል፤ የእነሱን ስራ ይሰራላቸዋል፡፡ ከእነሱ ጋር የሚሰራ አማራ አማራን ተረት ለማድረግ ተግቶ እየሰራ እንደሆነ ይወቀው፡፡ ግን ግን አንድ ቀን ሲገባው እየየ ብሎ ያለቅሳል፡፡ እኔ የምፈራው ወደህዝባቸው ተመልሰው በሚያለቅሱበት ጊዜ ሁሉም ከቁጥጥር ውጭ ሆኖ ምንም መፍትሄ ማምጣት እንደማይችሉ እንዳይሆኑ ነው፡፡ ከረፈደ በኋላ ለቅሶ ትርፉ ቅንድብ ማሳበጥ ብቻ ነው፡፡
እንግዲህ ጎንደር ወርቅ አበድሮ ጠጠር እንዲህ ተመለሰለት

መለክ ሐራ ከቤተ አማራ
ጎንደር ቤተ አማራ