Bete Amhara

Bete Amhara

Thursday, July 16, 2015

ወያኔ አማራ ስለሆንኩ ቆለጤን የሚቀጠቅጠኝ ስለሚወደኝ ነው አይነት ነገር

ወያኔ አማራ ስለሆንኩ ቆለጤን የሚቀጠቅጠኝ ስለሚወደኝ ነው አይነት ነገር

ትናንትና ዜና ሳፈላልግ የወገኖቸን ስም ዝርዝር በሞት ባህር መዝገብ ሰፍሮ አየሁት፡፡ ከነዛም አንዱ ደፈር ያለ ወንድሜ ቆለጡን እንደኮርማ መቀጥቀጡን ለህዝብ አሳየ፡፡ ቆለጡን የተቀጠቀጠው አማራ በመሆኑ እና ዘሩ መጥፋት እንዳለበት እየተነገረው እንደሆነ አስረዳ፡፡ ይህ ድርጊት ሽህ ጊዜ የተደጋገመ ነው፡፡ እኔ ራሴ በአንድ ወታደራዊ ካምፕ ያየሁትን ልንገራችሁ፡፡ አንድ መኮንን እያዞረ አሳየኝ፡፡ ያየሁትን ባላይ ይሻለኝ ነበር፡፡ ምድር ቤት ውስጥ እንደበረዶ እንዲቀዘቅዝ ተደርጎ የተሰራ ቤት አሳየኝ፡፡ ለትንሽ ደቂቃ መቆም እንኳ ፈተና ነው፡፡ ኩርምት ብለው የተቀመጡ እስረኞች አየሁ፡፡ ውስጡ ቀዝዛ ቆሻሻ ውሃና ጭቃ ሞልቶበታል፡፡ ከዛ ውስጥ የሚንበላወሱ ሰዎች አየሁ፡፡ መጀመሪያ ምነው ወደዚህ ቦታ ባልመጣሁ አልኩ፡፡ መኮንኑ ቃል በቃል እንዲህ አለኝ “እነዚህ የታሰሩት አማሮች ናቸው፤ በየትኛውም ክፍለ ጦር የአማሮች እስር ሁኔታ እንደዚህ ነው፡፡” ሞት እስካንገታቸው ያሰጠማቸውን አማራ ወገኖቸን በዛ እስር ቤት ውስጥ ፊታቸው ቆሜ አየሁ፡፡ መኮንኑ ቀጠለ “የሚተርፉት ጥቂት ናቸው፤ ቢተርፉም ከእንግዲህ ሰውኛ ኑሮ አይኖራቸውም፡፡” ይህ በየለቱ በአማራ ላይ የሚደረገው ግፍ ነው፡፡ ወደዛ አልገባም፡፡ ትናንትና በሰማሁት ነገር ግን ድጋሜ በጣም ተረበሽኩ፡፡ ከዚህ በፊት ካየሁት ሁኔታ ጋር ተደበላለቀብኝ፡፡

ይህንን እንደኮርማ የመቀጥቀጥ ዜና አንዱ ፌስቡክ ላይ ለጥፎ አየሁ፡፡ ከስሩ አንድ የአማራ ስም ያለው ሰው “እንደዚህ የምትጽፈው ህዝብ ከህዝብ ልታጣላ ነው” አለ፡፡ ሌሎችም የአማራ ስም ያላቸው ሰዎች ተመሳሳይ ነገር ጽፈው አየሁ፡፡ ለራሴ አንገቴን ጉልበቴ ውስጥ ከትቸ አዘንኩ፡፡ ይህ ህዝብ እዲነቃ ግን ምን እናሳየው? እውን ከዚህ በላይ ህዝብ ከህዝብ መጣላት አለ? በርግጥ አማራ ላይሆኑ ይችላሉ እነዚህ ሰዎች፡፡ ግን አሁንም ብዙ ያልነቃ እና ይህንን ሊረዳ ፍላጎት የሌለው አማራ የትየለሌ እንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ ይህ ድርጊት እንዲሰቀጥጥህ እኮ አማራ መሆን አይጠበቅብህም፡፡ ሰው ብቻ መሆን ነው የሚጠበቅብህ፡፡ በራስህ ሊደረግ የማትወደውን በሌላው ላይ አታድርግ የሚለውን ፍልስፍና ማወቅ ብቻ በቂ ነበር፡፡ ግን ይህ አማራ ምንኛ ያልታደለ ቢሆን ነው አማራ እንኳ የማያዝንለት? አንዳንድ ጊዜ ምናለበት ሁላችንም ድንጋይ ልብ በሆንን እና ሲያጠፉን ለምን ብለን ሳንጠይቅ በጠፋን እላለሁ፡፡ በአማራነተህ ቆለጥህን ቀጥቅጦ መካን ከማድረግና ከማሰቃየት እንዲሁም ከመስደብ በላይ ምን በደል አለ? ጠብ የሚባለው ከዚህ በላይ ምንድነው!? 

ግን በአማራ ልጆች ላይ ለምንድነው ይህ ሁሉ በደል የሚፈጸምባቸው ብለን እንጠይቅ እስኪ፡፡ ክሱ እንደሚስረዳው “በአሸባሪነት” ስለተጠረጠሩ ነው፡፡ ቁም ነገሩ ግን አማራ አለም ከተፈጠረ ጀምሮ የአሸባሪነት ስነልቡና የሌለው ጨዋ ህዝብ መሆኑ ነው፡፡ እጅግ ሰላም ወዳድ እና ሰው አክባሪ ህዝብ ነው፡፡ አሁን ግንቦት 7፤ መኢአድ፤ ሰማያዊ እና የቀድሞው አንድነት ፓርቲ አባላት በመሆናቸው የሚቀጠቀጡት አማሮች አሸባሪዎች ስለሆኑ አይደለም፡፡ እነዚህ የአማራ ልጆች የጠየቁት ጥያቄ ቀላል ነው፡፡ እኛም አገራችን ነው፤ በጋራ አገራችንን እናሳድግ፤ ዜግነታችን አይገፈፍ፤ አለም ወደደረሰበት የስልጣኔ ደረጃ ለመድረስ መንገድ እንጀምር እና ወዘተ ነው፡፡ ሲጨመቅ የሰለጠነ ሰው እንሁን ነው ያሉት፡፡ ይህ ግን አማራን ካላጠፋ እንቅልፍ ባይኑ ለማይዞረው ወያኔ ሽብር ነው፡፡

በዛም አለ በዚህ የአማራ ዘር እየጠፋ ያለው ከትግራይ በበቀሉ ወያኔዎች ነው፡፡ ከሰማይ ባለ በማንኛውም የሽብር ምክንያት የታሰረ ማንኛውም አማራ አሸባሪ አይደለም፡፡ ሰላም ወዳድ እና ለአገሩ ቅን የሚመኝ ነው፡፡ እነዚህ አማሮች ትግራይ ሄደው አላሸበሩም፡፡ በትንሹ በራሳቸው በአማራ አገር በሰላም መኖር ይችላሉ፡፡ የአማራን አገር የወረረው ወያኔ ነው “አሸባሪ” እያለ የሚያጠፋቸው፡፡ የሰው አገር በወረራ ይዞ በተወረረው የአማራ አገር ዜጋ ተሸበርኩ ማለት ራሱ በምን ቋንቋ እንደሚገለጽ አላውቅም፡፡ ለዛውም አብረን በሰላም እንኑር ስለተባለ ብቻ፡፡ አገሬን ለቅቀህ ውጣ አልተባለ፡፡ እንደ አገር አስብና አብረን እንኑር ብቻ ነው የተባለው፡፡ 

የወያኔን የአማራ ጥላቻ እና ጭካኔ ሳስበው በጣም ያስደነግጠኛል፡፡ ጣልያን ተመሳሳይ የአማራ ጥላቻ እንደነበረው ተመዝግቧል፡፡ አማራን በተለያየ መንገድ በተለያየ ቦታ አጥፍቷል፡፡ ግን የዘር ፍሬ ቀጠቀጠ የሚል ታሪክ አላነበብኩም፡፡ አማራን አምካኝ መርፌ ስለመውጋቱ አላነበብኩም፡፡ በርግጥ ዘሩ እንዳቀላቀልበት ኮንዶም ተጠቅሟል ሲባል ሰምቻለሁ (እርግጠኛ አይደለሁም)፡፡ ይህ ከሆነ ጣልያን ከወያኔ በስንት ጣእሙ ማለት ነው፡፡ ያ ኮንዶም ሲጠቀም፤ ይሄ ግን ማህጸንን ፍሬ አልባ ያደርጋል፤ የወንድ ብልትን ይቀጠቅጣል፡፡ የወያኔ የአማራ ጠላትነት እስካሁን በታሪካችን አይተነው የማናውቀው እና ጣልያንን የሚያስንቅ ነው፡፡

ነገሩ ታሪክ ራሱን ሲደገም መሆኑ ነው፡፡ መጽሀፉ በእጀ ስለሌለ ቃል በቃል አላስታውሰውም ግን የታሪኩ አንድምታ ይታወሰኛል፡፡ እንዲህ ሆነ፡፡ ስሁል ሚካኤል ከትግሬ መጥቶ በጎንደር ንጉሱን በሻሽ አንቆ ገድሎ የኢትዮጵያን መንግስት ጣለ፡፡ ከዛም ፈላጭ ቆራጭ ሆነ፡፡ አንድ ጊዜ ታዲያ ወታደሮቹ ሁለት የአማራ ሰዎችን ይይዙና ቆዳቸውን እስከነነፍሳቸው ይገፏቸዋል፡፡ በገፈፉት ቆዳቸውም አሸዋ ይቋጥሩበት እና ቆዳቸው ለተገፈፈው ሰዎች ያሸክሟቸዋል፡፡ አሸክመውም ይነዷቸዋል፡፡ ይህን የሰማ የላስታ፤ የጎጃምና የጎንደር ሰው ታዲያ ሆ ብሎ ጎንደርን አስጨንቆ ከበበና ስሁል ሚካኤልን እንዳይጥ ጨፍጭፎ ገደለው፡፡ ይህም ማለት የዚህ የጭካኔ ነገር ከጥንትም የነበረ መሆኑን ያሳያል፡፡ አሁንም ትግሬን ስለምትጠላ የምትሉ አማሮች ትኖራላችሁ፡፡ ነገር ግን ሀቅ ትግሬን አይጠላም ወይም አይወድም፤ እንዳለ በእውነትነቱ ይተላለፋል እንጅ፡፡ ባለፈው ፖስት የአጼ ዮሐንስን ጭካኔ ጽፌ ነበር፡፡ በተለይም የአማራን አንገት፤ ምላስ፤ እጅና እግር በጭካኔ ይቆርጥ እንደነበር ታሪክ የሚያወሳውን እውነት አስቀምጨ ነበር፡፡ በተለይ ንጉሰ ነገስት አጼ ተክለ ጊዮርጊስን ከማረከው በኋላ አይኑን መንቅሮ አውጥቶ መሬት ላይ እንደጣለ አንብበናል፡፡ ስሁል ሚከኤልም የሰው ቆዳ ገፎ ስልቻ ሰርቶ እስከነፍሳቸው ቆዳቸው ተገፎ የነበሩ ሰዎችን አሸክሞ መንዳቱን አየን፡፡ ወያኔ ለአርባ አመት የአማራን የዘር ፍሬ እንደሚቀጠቅጥ እና የሴትን ልጅ ጡት በኤሌክትሪክ እንደሚያቃጥል እንሰማለን፡፡ እንግዲህ የዚህን የጭካኔ ምንጭ ለመመርመር ሶስት ምስክር በቂ መሰለኝ፡፡ ለምንድነው በአማራ ላይ ከጥንት ጀምረው እንዲህ የሚጨክኑት የሚለውን በየህሊናችሁ መርምሩ፡፡ ልብ በሉ! የዚህ መልስ እኔን መስደብ ላይ አይደለም ያለው፡፡

መለክ ሐራ ከቤተ አማራ