Bete Amhara

Bete Amhara

Wednesday, July 15, 2015

የረር= አዲስ አበባ

የረር= አዲስ አበባ
==========
ሸዋ ከላሊበላ ቀጥሎ የተቋቋመች የአማራ ማረፊያ ናት፡፡
በላሊበላ ብዙ ዘመናት በልጽገው ኖሩ፡፡ ከዛ ወደ ሸዋ መጡ፡፡
ሸዋ ላይም ዋና ከተማቸውን መሰረቱ፡፡ የአሁኗ አዲስ አበባ
ለሁለተኛ ጊዜ ነው የአማራ ከተማ የሆነችው፡፡ ከላሊበላ
መጥተው የመሰረቷት ከተማ አዲስ አበባ ነበረች የረር በሚል
ስም፡፡ አዲስ አበባና አካባቢዋ እስከ ልብነ ድንግል ሽንፈት
ድረስ የአማራ ዋና ከተማ ነበረች፡፡ በተለይ አሁን ከአዲስ አበባ
ምስራቅ የሚገኘው የረረ ለረጅም ዘመናት ዋና ከተማ ነበር፡፡
ከአዲስ አበባ ሰሜን ያለው የአሁኑ እንጦጦ ራጉኤል የአማራ
ዋና ከተማ ነበር፡፡ ስለዚህ አንዳንዶች በስህተት ወይም ታሪክን
ካለማወቅ ወይም ሆነ ብለው የራሳቸው ለማድረግ
እንደሚያልሙት የኦሮሞ ወራሪዎች ዝባዝንኬ በአጼ ምኒልክ
የተመሰረተች አይደለችም፡፡ አዲስ አበባና አካባቢዋ ከይኩኖ
አምላክ ጀምሮ እስከ ልብነ ድንግል ድረስ በገደምዳሜው
ለሶስት መቶ አመት የአማራ ዋና ከተማ ነበረች፡፡ አጼ ምኒልክ
እንጦጦ ላይ ከተማ የመሰረቱት የአምደ ጽዮንን ከተማ ፈለግ
በመከተል ነው፡፡ ራጉኤል ያለው ዋሻ የአምደ ጽዮን ግምጃ ቤት
ነበር፡፡
ስለሆነም አዲስ አበባ አንዴ እንጦጦ ላይ፤ ሌላ ጊዜ የረር ላይ፤
ሌላ ጊዜ ተጉለት ላይ እየተዘዋወረች የአማራ ከተማ ሆና
አገልግላለች፡፡ አጼ ምኒልክ አካባቢውን እንደገና ነው
የአባቶቻቸውን ባድማ ታሪክ ለመመለስ ከተማ ያደረጉት፡፡ ከዛም
እቴጌ ጣይቱ የየረርን ከተማነት መልሳ በቦታው ተከለች፡፡
ስለዚህ አዲስ አበባ ሁለት ጊዜ የአማራ መዲና ሆነች፡፡